Saturday, 24 August 2013 11:13

“መኤኒት” ረዥም ልቦለድ ተመረቀ “ደንዲ የግዞት አምባ” ነገ ይመረቃል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(1 Vote)

የመኤኒት ብሄረሰብን የግጭት አፈታት ባህል በመንተራስ በአንዱአለም አባተ የተደረሰው “መኤኒት”ረዥም ልቦለድ መፅሀፍ የዛሬ ሳምንት እንደተመረቀ “አቢሲንያ የስነጥበብና የሞዴሊንግ ማሰልጠኛ ተቋም” አስታወቀ፡፡ መፅሀፉ ከጧቱ 3 ሰዓት አምስት ኪሎ በሚገኘው ብሄራዊ ሙዚየም ሲመረቅ፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው መፅሀፉን የተመለከተ ዳሰሳ፣ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና አቶ ገዛኸኝ ፀጋው ግጥሞች፣ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ እና ደራሲ ደሳለኝ ስዩም ከመፅሃፉ ቅንጭብ እንዳቀረቡ እንዲሁም የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ፕሬዝዳንት ደራሲና ሃያሲ ጌታቸው በለጠ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ ገብረፃዲቅ ሀጎስ በክብር እንግድነት እንደተገኙ ማወቅ ተችሏል፡፡ ደራሲው አንዷለም አባተ (ያፀደ ልጅ) የማስትሬት ዲግሪ መመረቂያ ፅሁፉን በብሄረሰቡ የግጭት አፈታት ባህል ላይ እንደሰራና የአቢሲንያ ተቋም መምህር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1832 times