Print this page
Saturday, 17 August 2013 12:34

“የሌ/ኮ መንግስቱ ምስጢሮች” ዛሬ ለንባብ ይበቃል

Written by 
Rate this item
(12 votes)

በቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም የቤተመንግስትና የስራ ህይወት ዙሪያ የተፃፈው “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጥሮች” የተሰኘ መፅሀፍ ዛሬ ከማተሚያ ቤት ወጥቶ ለንባብ እንደሚበቃ አዘጋጁ አስታወቁ፡፡ የቀድሞው ልዩ ኃይል አባል እና የፕሬዝዳንት መንግስቱ አጃቢ በነበሩት እሸቱ ወንድሙ ወልደስላሴ የተፃፈው ባለ 120 ገፅ መፅሃፍ ዋጋ 35 ብር ከ45 ሳንቲም ነው፡፡ ለ14 ዓመታት በልዩ ጥበቃነት የሰሩት የመፅሃፉ አዘጋጅ፤ ካሁን ቀደም “ህይወት በመንግስቱ ቤተመንግስት” በሚል ርዕስ ሁለት ቅፅ መጻሕፍትን ያሳተሙ ሲሆን ባሁኑ መፅሀፍ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል መንግስቱ የ1981ዱ መፈንቅለ መንግስት አድራጊዎችን ምን እንዳሏቸው፣ ፕሬዝዳንቱ በትረመኮንናቸው ላይ ብእር መሰል ሽጉጥ እንዲሰራላቸው መጠየቃቸው ወዘተ…ይገኝበታል፡፡

Read 4224 times
Administrator

Latest from Administrator