Saturday, 17 August 2013 11:59

....ከቤተሰብና ጉዋደኛ ጋር ውይይት ማድረግ.....

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(4 votes)

ጥናት በተደረገባቸው የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ እና የመሰናዶ ትምህርት ተከታታይ ሴቶች ዘንድ ፡-
ወሲባዊ ድርጊት ለመጀመሪያ ጊዜ ሲፈጸም እርግዝና ሊከሰት እንደሚችል የሚያውቁ ተማሪዎች 8.2 ኀናቸው፡፡
ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል መወሰድ የሚገባቸውን መከላከያዎች በሚመለከትም ትክክለኛው መረጃ ያላቸው 5.6 ኀ ብቻ ናቸው፡፡
Yohannes A. (Mekelle University, College of Health Sciences, Department of public health)
ከላይ የተመለከተውን መረጃ ያገኘነው በሰሜን ኢትጵያ በመቀሌ የተደረገ ጥናት በአቶ ዮሐንስ ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ አማካኝነት የቀረበ ነው፡፡ የስነተዋልዶ ናንና ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል በሚያስችል ሁኔታ እውቀትን ለመገብየት ወጣቶች ከቤተሰባቸወና ኝጉዋደኞቻቸው ጋር መምከር አለባቸው ሲሉ ያንሄዱትን የዳሰሳ ስራራ ወደ አማርኛ በመመለስ ለንባብ አቅርበናል ፡ ይህ ጥናት ከሚያሳየው ውጤት በመነሳት አንባቢዎች የየራራሳቸውን እርምጃ እንደሚወስዱ አምዱ ይማመናል፡፡
እንደአቶ ጥናቱ መረጃ አለምአቀፋዊውን የህዝብ ቁጥር 1.2 ቢሊዮን ያህሉን የሚጋሩት በእድሜያቸው ከ15-24 የሚደርሱ ወጣቶች ናቸው፡፡..፣ዛጨ.. ወጣቶች በአለም ላይ በተለያዩ የህይወት አጋጣሚዎች የሚፈተኑ ከመሆናቸው ጋር በተያያዘም ለተለያዩ የስነ ተዋልዶ ና ችግሮችና ላልተፈለገ እርግዝናም ለመጋለጥ ቅርብ ናቸው፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ በየአመቱ ከሚኖሩ ወሊዶች 11 %ዴ..ክኽ በእድሜያቸው ከ15-19 አመት የሚሆኑ ሴት ልጆች የሚወልዱት ሲሆን ይህም ወደ 95 %የሚሆነው በታዳጊ አገሮች ውስጥ የሚከሰት ነው፡፡
በሌላም በኩል ወደ 2.5/ ሚሊዮን የሚሆነው ማለትም በታዳጊ አገሮች ውስጥ የሚኖረው ደህንነቱ ያልተጠበቀ ውርጃ በእድሜያቸው ከ20/አመት በታች በሆኑ ሴት ልጆች የሚፈጸም ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በእድሜያቸው ልጅ የሆኑ ሴቶች እርግዝና በሚያጋጥማቸው ጊዜ ከእርግዝናው ጋር በተገናኛ ለሚፈጠር ሌላ የጤና ችግርም እንደሚጋለጡ እና የጽንስ መቋረጥ ሊገጥማቸው እንደሚችል እሙን ነው፡፡ ቀጥሎ የተመለከቱትን ነጥቦች ጥናቱ እንደማሳያ ..ፐቭቨዩቓም፡፡
የልጅነት ባህርይ -
ሴት ልጆች የልጅነት ባህርይን ባልተላቀቁበት እድሜያቸው ለወሲብ ድርጊት ቢጋለጡ እርግዝና ሊከተል ይችላል፡፡ ልጅን መውለድ አብሮት የሚመጣ ኃላፊነት እንደሚሆንም ግልጽ ነው፡፡ ልጅን ተንከባክቦ ናውን ብቆ ትን በተገቢው አጥብቶ ማሳደግና ሙሉ በሙሉ ንነቱን መንከባከብ ፣ እድገቱን መከታተል የቤተሰብ በተለይም ሁልጊዜም ለልጁ ቅርብ ወደሆነችው እናት ያዘነብላል። ይህንን ኃላ ፊነት ለመወጣት ዝግጁ ባልሆኑበት እድሜ እርግዝና ሲከሰት ልጆቹ በግልጽም ይሁን በድብቅ ጽንሱን ወደማቋረጥ እንደሚያዘነብሉ እሙን ነው፡፡ ለተፈጠረው ችግር መፍትሔ የሻቱ መስሎአቸው በሚወስዱት እርምጃ ወይንም ጥንቃቄ በጎደለው መንገድ ወሲብ በመፈጸማቸው እና ጥንቃቄ የጎደለው ጽንስ ማቋረጥን ቢተገብሩ እና ለስነተዋልዶ ና ጉደለት ቢጋለጡ ከቤተሰብ እና ኝጉዋደኞቻቸው ድብቅ በሆነ መንገድ ጉዳት ላይ ሊወድቁ የሚችሉበት አጋጣሚ ይፈጠራራል፡፡
ሴት ሕጻናቱ በእንደዚህ ያለው አጋጣሚ በትምህርት ከሌሎች ጉዋደኞቻቸው ዝቅ ወደ ማለት ስለሚያዘነብሉ ተስፋ ወደመ ቁረጥ እና እራራሳቸውንም ወደመጥላት ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ ምናልባትም ትምህርታቸውንም አቋርጠው ልጁን እንዲወልዱ እንኩዋን ቢደረግ ፈቃደኛ ሆነው እንደእናት ተንከባክቦ የማሳደግ ጥረቱ እምብዛም አይታይም፡፡
በስነተዋልዶ ና ላይ መነጋገር፡-
ጥናቱ እንደሚጠቁመው በኢትዮጵያም ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ በስነተዋልዶ አካላት ላይ የተመሰረተ ንግግር ወይም ውይይት ማድረግ እንደነውር የሚቆጠርበት አጋጣሚ አለ፡፡ በስነተዋልዶ አካላት ላይ መነጋገር ካልተቻለ ደግሞ ሊደርስ በሚችለው የጤና ጉዳይ እና ሊደ ረግ ስለሚገባው ጥንቃቄ መነጋገር አስቸጋሪ ይሆናል። በስነተዋልዶ አካላት ና ላይ በግልጽ መነጋገር ማለት ግን የጤና ችግር ከመፈጠሩ አስቀድሞ መፍትሔ ለመሻት የሚያስችል እው ቀትን ለማግኘት የሚረዳ እና ከራራስም አልፎ ለሌሎችም መምከር የሚያስችል ንቃተ ሕሊናን ማዳበር የሚያስችል ነው፡፡
ሴቶች በስነተዋልዶ ና ንቃተ ሕሊናቸው የመዳበሩ አሰፈላጊነት ከሚታይባቸው ነጥቦች መካከለ የቤተሰብ እቅድ ዘዴ ወይንም ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከል አንዱ ነው፡፡ ሴቶች ልጆችም ሆኑ የትዳር ወይንም የፍቅር ጉዋደኞቻቸው ልጅ መውለድ የሚቻልበትን ጊዜ አስቀድሞ በመመካከር ወስነው ልጅ መውለድ የሚገባቸው ሲሆን ከዚያ ውጭ ከሆነ ግን በግልጽ ካለመነጋገር ወይንም በመተፋፈር አላስፈላጊ ለሆኑ ችግሮች ሊጋለጡ ይችላሉ። ከነዚህም መካከል፡-
ላልተፈለገ እርግዝና መጋለጥ፣
ጥንቃቄ የጎደለው ጽንስ ማቋረጥ፣
በልጅነት ልጅ መውለድ፣
የልጅነት ባህርይ ስለሚኖር ወላጅነትን የመቀበል ችግር፣
ትምህርትን ማቋረጥ እና ሕይወትንም እስከማጣት ለሚያደርስ ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ፡፡
ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል በሚያስችሉ ነጥቦች ላይ የተለያዩ ጥናቶች በአገራራችን መካሄዳቸው እውን ቢሆንም በአብዛኛው በድርጊት ላይ ያተኮሩ እና በአፋጣኝ የእርግዝና መከ ላከያ ወይንም Emergency contraceptive ላይ ያተኮሩ ናቸው ፡ እስከአሁን ድረስ በተደረጉ ጥና ቶች በወላጆች እና በጉዋደኛሞች መካከል በስነተዋልዶ ና ጉዳይ ላይ በተለይም የእርግዝና መከ ላከያን በሚመለከት ሊኖር የሚገባውን የእርስ በእርስ ውይይት በሚመለከት ምንም የተደረገ ጥናት የለም ማለት ይቻላል ይላል ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የቀረበው ጥናት፡፡
ይህንን ርእሰ ጉዳይ በመቀሌ ከ20/ ሺህ በላይ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ እና በመሰናዶ ትምህርት በመማር ላይ ባሉ ተማሪዎች አካባቢ ጥናት የተደረገ ሲሆን ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል 11/አስራራ አንድሺህ የሚሆኑት ሴት ተማሪዎች እንደሆኑ ጥናቱ ይጠቁማል፡፡ ከእነዚህም መካከል ለጥናቱ በናሙናነት የተመረጡት ከየትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ወደ 845/የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች ናቸው። በቤተሰብና በጉዋደኛሞች መካከል ሊደረግ ስለሚገባው ግልጽ ውይይት በጥናቱ ወቅት ከታዩ አንዳንድ ለሴት ተማሪዎቹ ምቹ ያልሆኑ ነጥቦች መካከል፡-
የትምህርት እና የማህበራራዊ አኑዋኑዋር፣
የወላጆች በትክክል ከተማሪዎች ጋር አለመናበብ፣
በተማሪዎቹ መካከል ያለ ወሲባዊ ባህርይና የስነተዋልዶ ና ሁኔታ መለያየት፣
በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን የሚተላለፉ መልእክቶች ፣
ከወላጆች ወይንም ከጉዋደኞች ጋር በወሲብና ስነተዋልዶ አካል ዙሪያ ውይይት አለማድረግ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡
በጥናቱ ከታየው ውጤት መረዳት እንደሚቻለው ከተሳታፊዎቹ ውስጥ አንድ አምስተኛ (171)የሚሆኑት አስቀድሞኣኽ፣ኽጋ የወሲብ ጉዋደኛ ያላቸው ሲሆን ሶስት አራራተኛው 127ግን በትምህርት ቤት ውስጥ ጥናት ከመሳሰለው ጋር በተያያዘ የወሲብ ጉዋደኛ እንዳፈሩ ታውቆአል፡፡ ወሲብ በመፈጸም ረገድም ገሚሶቹ አስቀድሞኣኽ፣ኽጋ የጀመሩ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ በትምህርት ቤት ለጥናት በሚል ሰበብ ካፈሩዋቸው ጉዋደኞቻቸው ጋር መጀመራራቸውን መስክረዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል ወደ 15 % የሚሆኑት አስቀድሞኣኽ፣ኽጋ አርግዘው እንደሚያውቁ ከነዚህም ወደ 90 % የሚሆኑት ውርጃን እንዳከናወኑ ገልጸዋል፡፡
ያልተፈለገ እርግዝናን በተመለከተ ተማሪዎቹ ሲጠየቁ የመለሱት በእርግጥ ቢያንስ ስለ አንድ አይነት የመከላከያ ዘዴ ሰምተው የሚያውቁ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል ያለው መንገድ የወንዶች ኮንዶም ብቻ አንደሆነ የሚያውቁ መሆኑን ለጥያቄው መልስ ሰጥተዋል፡፡ በጥናቱ ከተሳተፉት መካከል ያልተፈለገ እርግዝና መከላከያን በመርፌ ወይንም በእንክብል መልክ እንደሚሰጥ የሰሙ መሆኑን የገለጹ ያሉ ቢሆንም ወደ 80 %ኛትሽ ሆኑት አገልግሎቱ የሚሰጠው ከአንድ ስፍራራ ብቻ መሆኑ እንደሚያውቁ ገልጸዋል፡፡ ወሲባዊ ድርጊት ለመጀመሪያ ጊዜ ሲፈጸም እርግዝና ሊከሰት እንደሚችል የሚያውቁ ተማሪዎች 8.2 % ናቸው፡፡ ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል መወሰድ የሚገባቸውን መከላከያዎች በሚመለከትም ትክክለኛው መረጃ ያላቸው 5.6 %ብቻ ነበሩ፡፡
በአጠቃላይ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ እና በመሰናዶ ትምህርት ላይ በነበሩ ሴት ተማሪዎች ላይ በተደረገው ጥናት ያልተፈለገ እርግዝናን መከላልን በሚመለከት የነበራራቸው ግንዛቤ እጅግ አሳሳቢ ሆኖ ነው የተገኘው፡፡ በጥናቱ ለናሙና ከተወሰዱት ተማሪዎች መካከል ስለሁኔታው በቂ እውቀት ያላቸውና እራራሳቸውን ካልተፈለገ እርግዝና መከላከል የሚችሉት በጣም ጥቂት ሆነው ነወ የተገኙት ምንም እንኩዋን መልእክቱ በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን የሚተላለፍ ቢሆንም ቀጣይነት ባለው መንገድ እና ንቃተ ሕሊናን በሚያዳብር መልኩ መሆኑ አጠራራጣሪ ከመሆኑም ባሻገር መልእክቱ ምን ያህል ሴት ተማሪዎቹ ጋር ደርሶአል የሚለውን ለመገመት አስቸጋሪ ነው፡፡
ጥናቱ በማጠቃለያው ያመላከተው በመላ ሀገሪቱ ባሉ ወጣቶች ዘንድ ያለው ሁኔታ በቀጣይነት ሊጠና እንደሚገባውና እንዲሁም ቤተሰብ ለልጆቹ ቅርብ በመሆን በስነተዋልዶ አካላት ጉዳይ ላይ ግልጽ ውይይት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ ትምህርት ቤቶችም በጉዋደኛሞች መካከል ለሚያስፈልገው የእርስ በእርስ ውይይት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ..ጭፐቨዩቓም፡፡ ወጣቶችም የሚገጥማቸውን ማንኛውንም ነገር በቅርብ ካለ ጉዋደኛ እንዲሁም ከቤተሰብ ጋር በግልጽ መወያየትን እንዲያምኑና እንዲተገብሩ ያስፈልጋል፡፡

Read 4949 times