Saturday, 03 August 2013 11:25

“የግጥም በጃዝ”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሁለተኛ ሻማ ረቡዕ ይለኮሳል

በወጣት ከያንያን ተቋቁሞ ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያን፣ ሙዚቀኞችና ሌሎች የጥበብ ባለሙያዎች የሚሳተፉበት “ግጥምን በጃዝ” ኪነጥበባዊ ዝግጅት፤ ሁለተኛ ዓመት ክብረ በዓሉን በመጪው ረቡዕ 11፡30 በብሔራዊ ትያትር እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ ላለፉት ሁለት ዓመታት ከቀረቡት ዝግጅቶች ላይ ተመርጠው የተሰናዱ ሥራዎች “ጦቢያ” በሚል ርዕስ በዲቪዲ የታተመ ሲሆን በ50 ብር ለገበያ እንደሚቀርብ ታውቋል።
በረቡዕ ዝግጅት ላይ በአንደበተ ርቱዕነታቸው የሚታወቁት መምሕር እሸቱ አለማየሁ በተመረጠ ርእሰ ጉዳይ ላይ ዲስኩር የሚያሰሙ ሲሆን ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ጌትነት እንየው፣ አበባው መላኩ፣ ግሩም ዘነበ፣ ምስራቅ ተረፈ፣ ምህረት ከበደ፣ ሜሮን ጌትነት፣ ደምሰው መርሻ እና ምንተስኖት ማሞ የግጥም ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 2347 times