በፈለቀ ካሳ ጥንድ ፕሮሞሽን የሚዘጋጀው የጥበብ ምሽት፣ የመጀመሪያ ዝግጅቱን ከትናንት በስቲያ ማታ ቦሌ በሚገኘው ሻላ አዳራሽ ቀረበ፡፡ በየወሩ አንድ ደራሲና አንድ ሙዚቀኛ የሚቀርቡበት ኪነጥበባዊ ዝግጅት የመግቢያ ዋጋ በግለሰብ 50 ብር ሲሆን ከዚሁ ገቢ በየወሩ ለአንድ ሕጻን 200 ብር በመመደብ አምስት ሕጻናትን ለመንከባከብና ለማስተማር ይውላል፡፡ የጥበብ ምሽቱ በኮሜዲ ዝግጅቶችም እንደሚታጀብ ለማወቅ ተችሏል፡፡