Saturday, 20 July 2013 10:54

ሰዓሊያን የጐዳና ትርዒት አቀረቡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የ“አለ ኪነጥበባት” ትምህርት ቤት ሰዓሊዎች ከ“ነፃ አርት ቪሌጅ” ጋር በመተባበር የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ስለ ሥዕል እና ቅርፃ ቅርፅ ያላቸው ግንዛቤ እንዲዳብር “ሰምና ወርቅ” የተሰኘ የጐዳና ላይ ትርዒት በማዘጋጀት የመነጋገርያ ሃሳብ አቀረቡ፡፡ ባለፈው ረቡዕ የቀረበው ዝግጅት በ”አለ ኪነጥበባት” ትምህርት ቤት ተጀምሮ ከአራት ሰአታት የከተማዋ ጉብኝት በኋላ የተጠናቀቀ ሲሆን አራት ኪሎ፣ ፒያሳ፣ ተክለሃይማኖት፣ ሜክሲኮ፣ ራስ መኮንን ድልድይ፣ መርካቶና ጃንሜዳን ያካተተ ነው፡፡ በጐዳና ትእይንቱ ሰዓሊ ታምራት ገዛኸኝ፣ ተስፋሁን ክብሩ፣ ዳንኤል አለማየሁ፣ ሙልጌታ ካሳ እና ለይኩን ናሁሰናይ እና ሌሎች ተሳትፈዋል፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን፣ ዶክተር ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ እና የውጭ አገር ኮሙኒቲ አባላት በክብር እንግድነት ተገኝተዋል፡፡

 

Read 1463 times