Saturday, 20 July 2013 10:52

“የጨረቃ ጥሪ” እና “ሉሲ ተሸጣለች” ለንባብ በቁ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በፊልም ባለሙያው ተስፋዬ ማሞ ወንድም አገኘሁ የተፃፈው “የጨረቃ ጥሪ” ወንጀል ነክ ረዥም ልቦለድ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ልቦለዱ ከ21 ዓመት በፊት የተፃፈ መሆኑን ደራሲው ገልጿል፡፡
በ1982 ለንባብ የበቃችው “ዕፀበለስ” የተሰኘች መፅሐፉ በአንባቢያን ዘንድ መወደዷ በፈጠረበት ግለት ተነሳስቶ “የጨረቃ ጥሪ” የተባለውን ሁለተኛ መፅሐፉን ቢፅፍም የህትመት ብርሃን ሳያይ መቆየቱን ተናግሯል፡፡
በኤችዋይ ኢንተርናሽናል ፕሪንቲንግ የታተመው ባለ 212 ገፅ ልቦለድ መፅሐፍ፤ ለኢትዮጵያ ገበያ በ50 ብር፣ ከኢትዮጵያ ውጭ ደግሞ በ15 ዶላር ይሸጣል፡፡ “ሉሲ ተሸጣለች” የተሰኘው ረዥም ልቦለድም ለንባብ የበቃው በዚህ ሳምንት ነው፡፡
በአንድነት አየለ ኃይሌ የተፃፈው ባለ 289 ገፅ መፅሐፍ፤ በአሀዱ ማተሚያ ቤት የታተመ ሲሆን ለሀገር ውስጥ በ44.96 ብር ፣ ለውጭ ሀገራት በ45 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡

Read 1664 times