Saturday, 13 July 2013 12:12

“መልክዐ ስብሀት” ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በደራሲና ሃያሲ አለማየሁ ገላጋይ አርታኢነት ሰላሳ ፀሐፍት ገጣሚያንና ሰዓሊያን በስብሐት ገብረእግዚብሔር ህይወትና ሥራ ላይ ያቀረቧቸው ፅሁፎች የተካተቱበት “መልክዐ ስብሀት” የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ሰኞ በ11 ሰዓት በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ አዳራሽ ይመረቃል፡፡ መፅሐፉ በደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ሥራና ህይወት ላይ የሚያተኩር እንደሆነ ታውቋል፡፡
ፅሁፎቻቸው በመፅሐፉ ከተካተቱ ፀሐፍት መካከል ሃያሲ አስፋው ዳምጤ፣ ቴዎድሮስ ገብሬ፣ ሌሊሳ ግርማ፣ አዳም ረታ፣ ኢዮብ ካሣ፣ ሚካኤል ሽፈራው፣ ነቢይ መኮንን፣ አልአዛር ኬ፣ አውግቸው ተረፈ የሚገኙበት ሲሆን ከሰዓሊያን ደግሞ በቀለ መኮንን፣ ፍፁም ውብሸት፣ ቴዲማን ተካትተዋል፡፡
መፅሐፉ ሲመረቅ ነቢይ መኮንን፣ ታገል ሰይፉ፣ በቀለ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ እና ሌሎችም ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡
“መልክዐ” በሚል ቅድመ ግንድ ተከታታይ መፅሐፍት ለመታተም መታቀዱንና “መልክዐ ፀጋዬ ገብረመድህን” በዝግጅት ላይ መሆኑን የገለፀው አርታኢው፤ ስለ ስብሃት የታተመው “መልክዐ ስብሐት” መድበል ሚዛናዊነቱን የጠበቀ እንዲሆን ጥረት መደረጉን ተናግሯል፡፡

Read 2850 times