በአለን ሌከን ተፅፎ አባተ መንግሥቱ የተረጐመው “ስኬታማ የጊዜ አጠቃቀም” እየተሸጠ ነው፡፡ በውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም ዙርያ የተፃፈው መፅሐፍ ኤችኬ ፐብሊሺንግ የታተመ ሲሆን ዋጋው 25 ብር ከ35 ነው፡፡የመጽሐፉን የአርትኦት ስራ ደራሲና ሃያሲ መስፍን ሃብተማርያም ነው የሰራው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የሮቢን ሻርማ “The Monk Who Sold His Ferrari” በብርሃኑ በላቸው “ራስን ማወቅ” በሚል ርዕስ ተተርጉሞ ለገበያ የበቃ ሲሆን በ35 ብርም እየተሸጠ ነው፡፡ በፋርኢስት ትሬዲንግ የታተመው መፅሐፉ፤ 176 ገፆች አሉት፡፡ መፅሐፉን መገናኛ አካባቢ የሚገኘው ዩኒቲ መፃህፍት መደብር እንሚያከፋፍል ታውቋል፡፡