በወይንሸት መርከቡ የተደረሱ አምስት አጫጭር ልቦለዶች የተካተቱበት “እኔና ቄስ ገንዘቤ” የአጫጭር ልቦለዶች መድበል ለንባብ በቃ፡፡ በመፅሐፉ “እኔና ቄስ ገንዘቤ” ባለ አራት ክፍል አጭር ልቦለድ እንዲሁም “ማትሪክ”፣ “አቢይ እና አባይ”፣ “ኮሌጅ” እና “ይድረስ ለፈጣሪ” የተሰኙ ሌሎች አጫጭር ልቦለዶች ተካተውበታል፡፡ 118 ገፅ ያለው መፅሐፉ ባናዊ ማተሚያ ቤት የታተመ ሲሆን ዋጋው ለሀገር ውስጥ 25 ብር፣ ለውጭ ሀገራት 10 ዶላር ነው፡፡ በሰሎሞን ታደሰ የተደረሱ ወጐችና እውነተኛ ታሪኮች የተካተቱበት “የሸገር ወጐች እና እውነተኛ ታሪኮች” መፅሐፍ እንዲሁ ለንባብ በቅቷል፡፡ በመፅሐፉ “የሸገር ወጐች”፣ “መጣንላችሁ ማሳጆች”፣ “የጨለሙ ታሪኮች በዱባይ” እና ሌሎች ታሪኮች ተካተዋል፡፡ ደራሲው ካሁን በፊት “ቦሌ ፒኮክ ጋ ጠብቂኝ” የተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ አብቅቷል፡፡ “የሸገር ወጐች” በ39.50 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል