Print this page
Saturday, 29 June 2013 10:54

ሄነሪ ካቪል በ “ማን ኦፍ ስቲል” ተደነቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“ማን ኦፍ ስቲል” በተባለው ፊልም ላይ የሱፐር ማንን ገፀባህርይ በብቃት በመተወን ሄነሪ ካቪል እንደተዋጣለት “ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር” ገለፀ፡፡ እንግሊዛዊው ተዋናይ ሄነሪ ካቪል ሱፐርማንን ለመምሰል ሲል 40 ፓውንድ ኪሎ ቀንሷል ያለው ዘገባው፤ ይህን ለማሳካትም ለ11 ወራት በሳምንት 12 ሰዓታትን የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማድረጉን አትቷል፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት ለእይታ የበቃው ፊልሙ፤ በመላው ዓለም ያስገባው ገቢ 400 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል፡፡

የሱፐር ማን ፊልሞች ተወዳጅነት በአሜሪካ ብቻ ተወስኖ ቢቆይም “ማን ኦፍ ስቲል” ከአሜሪካ ባሻገር በመላው ዓለም ተወዳጅነት በማግኘት የመጀመርያው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ዋርነር ብሮስ ለፊልሙ በጀት 225 ሚሊዮን ዶላር ያወጣ ሲሆን፤ የሱፐር ማን ገፀባህርይ በካርቱን ኮሚክ መፅሃፍ፤ በቲቪ ተከታታይ ፊልሞች እና እስካሁን በተሰሩ ፊልሞቹ ላለፉት 70 አመታት ዝናና ስኬትን ተቀዳጅቶ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ “ማን ኦፍ ስቲል” መታየት ከጀመረ በኋላ ከሱፐር ማን ጋር የተያያዙ የንግድ እንቅስቃሴዎች መሟሟቃቸውን የዘገበው “ብሉምበርግ ኒውስ” በበኩሉ፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሱፐር ማን ቲሸርቶች እና አሻንጉሊቶች እንደተቸበቸቡ ገልጿል፡፡

Read 2359 times
Administrator

Latest from Administrator