በሰሜን አሜሪካ ከሚገኘዉ ታዋቂዉ የፊልም ኩባንያ ከ”አባይ ሙቪስ” እና በርካታ ሀገርኛ ሲኒማ በመስራት ላይ የሚገኘዉ እና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሥራ ላይ የተሰማራዉ ኦክቴት ኮምፒዉተር ቴክኖሎጂ በመተባበር በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሚያዘጋጀዉን እና የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተመሰረተበትን የ30ኛ ዓመት አከባበር ሥነ-ስርዓት ከሰኔ 23 2005 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30 2005ዓ.ም በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ሜሪላንድ ዉስጥ በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ኢትዮጵያዉያን እና ትዉልደ ኢትዮጵያን በሚገኙበትን ይከበራል፡፡በዚህም ዝግጅት ላይ ታዋቂ የሀገርችን አርቲስቶች የሙዚቃ እና የተለያዩ ባህላዊ እሴቶችን የሚያንጸባርቁ ዝግጅቶችን ያቀርባሉ፡፡ በዝግጅቱም ላይ በርካታ ታዋቂ ስፖርተኞች፣ ጋዜጠኞች የፊልም ባለሙያዎች በዝግጅቱ ላይ ይታደማሉ፡፡ ዝግጅቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡