Print this page
Saturday, 29 June 2013 10:40

“ጀንኖ” የተሰኘ አዲስ ፊልም ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በፋሲል አስማማው ተፅፎ በደረጀ ደመቀ የተዘጋጀው “ጀንኖ” የተሰኘ አዲስ ፊልም ዛሬ በሐዋሳ ከተማ እና በሌሎች ክልል ከተሞች ይመረቃል። በጵንኤል ፕሮሞሽንና ማስታወቂያ ድርጅት ፕሮዱዩሰርነትና በታምሩ ብርሃኑ ፕሮዳክሽን የተሠራው ፊልሙ፣ የሮማንቲክ ኮሜዲ ዘውግ ሲኖረው አልጋነሽ ታሪኩ፤እንቁስላሴ ወርቅ አገኘሁ፣ዘነቡ ገሠሠ፣ ደረጀ ደመቀና ተመስገን ታንቱን ጨምሮ ከ60 በላይ ተዋናዮች ተካፍለውበታል፡፡ ፊልሙ በሐዋሳው የሲዳማ ባህል አዳራሽ በሚመረቅበት በዛሬው ዕለት በዲላ፣ በሻሸመኔ እና በነገሌ ቦረና እንደሚመረቅ የፊልሙ ደራሲ ፋሲል አስማማው ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ በቅርቡም በአዲስ አበባ በሚገኙ ሲኒማ ቤቶች ይመረቃል፡፡

Read 2103 times
Administrator

Latest from Administrator