Saturday, 22 June 2013 12:19

የኮንሶ ባህላዊ ፌስቲቫል በመጪው ሳምንት ይጀመራል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(1 Vote)

የኮንሶ ባሕላዊ ቅርሶች በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓለምአቀፍ ቅርስ ሆነው የተመዘገቡበትን አንደኛ ዓመት በማስመልከት የተዘጋጀ ፌስቲቫል በመጪው ሳምንት እንደሚካሄድ በደቡብ ብሔራዊ ክልል ሰገን ዞን የኮንሶ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ከሰኔ 21 እስከ 23 በካራት ከተማ የሚካሄደውን ፌስቲቫል አስመልክቶ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ በሪቆ በላቸው ጉይታ ሲያስረዱ፣ የኮንሶን ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በመቀየር ከጎብኚዎች ፍሰት እንጠቀማለን ብለዋል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው ፌስቲቫል በሲምፖዚየም፣ በጎዳና ላይ የባህልና ጥበብ ትዕይንት፣ በመሠረተ ልማት ጉብኝትና በሌሎችም ዝግጅቶች የታጀበ ሲሆን ፌስቲቫሉ በየዓመቱ የሚከበር መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1828 times