Print this page
Saturday, 22 June 2013 12:18

“የአሲምባ ፍቅር” እና “ውጥንቅጥ” ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮጵያውያን የዲሞክራሲ እና የነፃነት ትግል ላይ ተንተርሶ የተፃፈው “የአሲምባ ፍቅር” መጽሐፍ ዛሬ እንደሚመረቅ ሜሮኢ መልቲሚዲያ አስታወቀ፡፡ 448 ገፅ ያለውን መጽሐፍ የደረሱት ካህሳይ አብርሃ ብስራት ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ እና ግንባር (ኢህአፓ/ኢህአሠ) ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ ተመስርቶ የተፃፈው መጽሐፍ የሚመረቀው መስቀል አደባባይ በሚገኘው የቀይ ሽብር ሰማዕታት ብሔራዊ ሙዚየም ነው፡፡ “የአሲምባ ፍቅር” በ100 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ በሌላ በኩል “ውጥንቅጥ” የተሰኘው የግጥም መጽሐፍ ነገ እንደሚመረቅ ገጣሚው አስታወቀ፡፡ ባምቢስ አካባቢ በሚገኘው ትልቁ ዮርዳኖስ ሆቴል የሚመረቀውን የግጥም መጽሐፍ የፃፈው ዮርዳኖስ ፍቃዱ ተክለማርያም ነው፡፡

Read 2213 times
Administrator

Latest from Administrator