Print this page
Saturday, 15 June 2013 12:21

“…ለእርጉዞች መነገር የሌለባቸው ነገሮች …”

Written by 
Rate this item
(10 votes)

“...ሁልጊዜ ጥሩ አስተያየት የሚሰጡኝን ሁለት ሰዎች በጣም እወዳቸዋለሁ፡፡ በሚያዩኝ ጊዜ ሁሉ ...ኦ...ዛሬ በጣም ጥሩ ነሽ፡፡ እርግዝናውም ቀለል ብሎሻል፡፡ ይሄ የሆድሽ ከፍታ እኮ ከትንሽ ጊዜ በሁዋላ ይቀላል፡፡ በተለይም ሊወለድ ሲል በጣም ይቀል ሻል፡፡ አይዞሽ የሚል አስተያየትን ከእነርሱ መስማት በጣም ያስደስተኛል ...ትላለች ፡፡በአሁኑ ወቅት እርግዝናዬ 34ኛ ሳምንቱን ይዞአል የምትለው ወይዘሮ፡ በተጨማሪም እንዲህ ትላለች፡፡ “… እኔ ለነገሩ በእርግዝናው ምክንያት በሚፈጠረው ሆርሞን ምክንያት ምንም ነገር ቢነገረኝ እንዳያናድደኝ ስለምጠነቀቅ ነው እንጂ እንኩዋንስ የማይሆን ነገር ተናግረ ውኝ ቀርቶ ደህናም ነገር ቢያወሩኝ በጥርጣሬ የምቀበል ሆኛለሁ፡፡ እስቲ በዚህ ጉዳይ የተለያዩ አባባሎችን ...ማለትም ከሰዎች የወሰድኩዋቸውን አንብቡ ብላለች አሊሰን ፋክለር...፡፡ ዶ/ር መብራቱ ጀምበር ባለፈው እትም ስለ ማህጸን ውጭ እርግዝና ያብራሩትን ካስነ በብናችሁ በሁዋላ አሊሰን ፋክለር በእርግዝና ጊዜ መነገር የሌለባቸው ያለቻቸውንና ከአገር ውስጥም ልምዳቸውን ያካፈሉንን አካተን ለንባብ እንላለን፡፡

“.....እንደሚታወቀው እርግዝና የሚፈጠረው በወንዱ ዘርና በሴቷ ዘር ግንኙነት መንስኤነት ነው፡፡ይህ በጤናማ መልኩ የተፈጠረ ከሆነ የሚገኘው በዘር ማስተላለፊያ ቱቦው ላይ ነው፡፡ በዚያም የተወሰነ ቀን ካሳለፈ በሁዋላ የተወሰነ የሰውነት ገንቢ ሕዋሳቶች ደረጃ ላይ ሲደርስ ወደ ዋናው የማህጸን ክፍል ውስጥ ይገባል፡፡ በማህጸን ውስጥም እርግዝናው እስኪጨርስ እና አድ ጎም ለመወለድ እስኪደርስ ድረስ ይቆያል፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ይህ ሂደት ሊዛባ ይችላል፡፡ በዚህም ሳቢያ ጽንሱ ወደ ማህጸን ከመሄዱ ይልቅ የተለያየ ቦታ በመቅረት ባለበት ቦታ እድገቱን ይጀምራል፡፡ በተለይም በዘር ማስተላለፊያ ቱቦው ጫፍ ወይንም መሃል አለበለዚያም ወደ ማህጸን ተጠግቶ ሊያድግ ይችላል፡፡ ከዚህም ውጭ ጽንሱ እንደተፈጠረ ዝም ብሎ ሆድ እቃ ውስጥ በመውደቅ ሞራ ላይ ወይንም አንጀት ላይ እና በመሳሰሉት አካላት በመጠጋት በዚያው እድገቱን ሊጀምርም ይችላል፡፡.. ከላይ ያስነበብናችሁ የማህጸን ውጭ እርግዝና እንዴት እንደሚፈጠር የሚያስረዳውን ባለፈው እትም ዶ/ር መብራቱ ጀምበር ያብራሩትን ነበር፡፡ በተለይም በሆድ እቃ ውስጥ ሰለሚኖረው ከማህጸን ውጭ እርግዝና ሲገልጹ፡- “...ከማህጸን ውጭ እርግዝና ከሁለት እስከ ሶስት ወር ድረስ አደጋ የሚከሰትበት ወቅት ነው፡፡

ነገር ግን በሆድ እቃ ውስጥ የሚያርፈው ከማህጸን ውጭ እርግዝና አልፎ አልፎ እስከመጨረሻው የእርግዝና ወቅት ድረስ ደርሰው በሰላም ልጆቻቸውን የተገላገሉ አሉ፡፡በእርግጥ እርግዝናው በማህጸን ውስጥ እንደሚኖረው እርግዝና ሳይሆን አስቸጋሪና ከበድ ያለ ነው፡፡ በሆድ እቃ ውስጥ ያሉ ሌሎች አካላት ጨጉዋራ፣ ጉበት...ወዘተእንዳሉ ሆነው እርግዝናው ግን ባገኘው ክፍት ቦታ ላይ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡ ዋናው ነገር የእንግዴ ልጁ የደም ስር ሊያገኝ እና ሊያድግ የሚችልበት ቦታ መሆን አለበት፡፡ እንግዴ ልጁ የሚመቸው ቦታ ላይ ካረፈ በሁዋላ ለልጁ ከእናቱ ደም ስቦ አጣርቶ በመመገብ እንዲያድግ ያደርገዋል፡፡ እርግዝናው በማህጸን ውስጥ ባለመሆኑ መጥፎ አጋጣሚ ነው ተብሎ ቢፈረጅም ልጁን በሰላም እስከመጨረሻው ጠብቆ መገላገል ግን እድለኝነት ይባላል፡፡ በእርግጥ ይህ ሁኔታ በቅርብ ጊዜ የተፈጸመ ሳይሆን በአሁኑ ጊዜ ያሉ ክኖሎ ጂዎች ባልነበሩበት ወቅት የነበረ አጋጣሚ ነው፡፡

በአሁኑ ጊዜ ግን አስቀድሞውኑ ጽንሱ የተፈጠረበት ስፍራ በምርመራ ስለሚታወቅ አደጋ ከማስከተሉ በፊት እርምጃ ይወሰ ዳል፡፡ አስቀድሞ በነበረው የህክምና ዘዴ ግን በሆድ እቃ ውስጥ የሚፈጠረው እርግዝና እስኪወለድ ድረስ ሊከሰት የሚችለውን አደጋ እንዳይደርስ ከመናፈቅ ባለፈ የሚደረግ ነገር አልነበረም፡፡ ጽንስ በማህጸን ውስጥም ሆነ በሆድ እቃ ውስጥ ሲረገዝ የራሱ የሆነ መሸፈኛ ይኖረዋል፡፡ ጽንስ በማህጸን ውስጥ ሲያድግ ላስቲክ መሰል በሆነ ስስ ሽፋን ውስጥ ሆኖ በሽፋኑ ውስጥ የሽርት ውሀ ከቦት ነው የሚያድገው፡፡ በእርግጥ ሽፋኑ እንደላስቲክ ስስ ሳይሆን ጠንከር ያለ እና ሞራ መሰል መልክ ያለው ነው፡፡ ይህ አፈጣጠር ጽንሱ በሆድ እቃ ውስጥም በሚፈጠ ርበት ወቅት በተመሳሳይ ሁኔታ ተሸፍኖ ስለሆነ ባለበት ቦታ ምንም ባእድ ነገር ሳያገኘው ሊያድግ ይችላል፡፡ ነገር ግን እርግዝናው ምን ያህል እንደሚቀጥል ማወቅ ስለማይቻል ዝም ብሎ እስከመጨረሻው መጠበቅ ያስቸግራል፡፡

ከማህጸን ውጭ በሆድ እቃ ውስጥ የተረገዘ ጽንስ የሚወለደው ካለምንም ችግር በኦፕራሲዮን ይሆናል፡፡ በማህጸን ውስጥ የተረገዘን ልጅ በኦፕራሲዮን ለማዋለድ በመጀ መሪያ የሆድ እቃ ከዚያ በሁዋላ ደግሞ ማህጸን ተከፍቶ ሲሆን እርግዝናው በሆድ እቃ ውስጥ ከሆነ ግን እንዲያውም በቀላሉ ሆድ እቃን ብቻ በመክፈት ማገላገል ይቻላል፡፡ የማዋለዱን ተግባር ልዩ የሚያደርገው ግን እንግዴ ልጁ በዚያው መቅረት ስለሚገባው ነው፡፡ የእንግዴ ልጅን ለማውጣት ትግል ከተፈጠረ ደም የመፍሰስ ነገር ስለሚከሰት አደጋ ላይ መውደቅን ያስከትላል፡፡ ስለዚህም እትብቱን ቆርጦ ልጁን ከማውጣትና አንባቢውን ከማጽዳት ያለፈ ምንም አይደረግም፡፡ እንግዴ ልጁ በዚያው እንዲጠፋ ይተዋል ፡፡ በማህጸን የተረገዘ ልጅ ሲወለድ የእንግዴ ልጁ በጥንቃቄ የሚወገድ እና ይቅር ቢባልም አደጋን የሚያስከትል ሲሆን በሆድ እቃ ውስጥ ግን ምንም ችግር ሳያስከትል በራሱ ጊዜ እንዲጠፋ ይደረጋል፡፡

ከማህጸን ውጭ የተረገዘ ልጅ እንቅስቃሴው ፊት ለፊት በቀላሉ የሚታይ ነው፡፡ ምክንያቱም በማህጸን ውስጥ እንዳለው ልጅ በሁለተኛ ደረጃ በማህጸን ግድግዳ ተሸፍኖ ስለማይገኝ ነው፡፡ በምጥ መውለድን በሚመለከትም በሆድ እቃ የሚኖር እርግዝና በትእግስት በሚጠበቅበት ዘመን በክሊኒክ በሚቆጠረው የጊዜ ቀመር በመመስረት በኦፕራሲዮን እንዲወለድ ይደረጋል እንጂ እንደ መደበኛው እርግዝና ምጥን መጠበቅ አይቻልም፡፡ ከማህጸን ውጭ እርግዝና በዘር ማስተላለፊያ ቱቦ ውስጥም ይሁን በሆድ እቃ ውስጥ ሲፈጠር አደጋ የሚያስከትልበት ሁኔታ መኖሩ እርግጥ ነው፡፡ በተለይም ከሁለት እስከሶስት ወር ድረስ ባለው ጊዜ ከሚከሰተው አደጋ ዋናው የደም መፍሰስ ነው፡፡ የዚህም ምክንያቱ ጽንሱ ያለበት ቦታ እስከመጨረሻው ስለማያሳድገውና መቀደድ ስለሚጀምር ነው፡፡

ይህንን ሁኔታ የሚያባብሰውም እርግዝና በሚፈጠርበት ጊዜ እርግዝናው ባለበት አካባቢ እርግዝናውን ለማሳደግ የደም ስሮች በብዛት ስለሚፈጠሩ ጽንሱ ያለበት ቦታ ሲፈነዳ ደም በኃይል እንዲፈስ ስለሚያደርግ ነው ፡፡ይህ የደም መፍሰስም ሴትየዋን እስከሞት ሊያደርስ የሚችል ነው፡፡ ከማህጸን ውጭ እርግዝናን አስቀድሞ መወቅ የሚቻልባቸው ምልክቶች አሉ፡፡ እርግዝናው መኖሩ ከተረጋገጠ በሁዋላ ከማህጸን ደም መፍሰስ ሊጀምር ይችላል፡፡ ከእምብርት በታች ባለው የሰ ውነት ክፍል ሕመም ሊኖር ይችላል፡፡ እግርን የመያዝ አይነት ስሜት ሊኖር ይችላል፡፡ እርግዝናው ውጥረቱ እየጨመረ ሲሄድ ከመፈንዳቱ በፊት የተገለጹት ስሜቶች ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡በእርግጥ ሌሎች የጤና ሁኔታዎችም ተመሳሳይ የህመም ምልክቶችን ሊያሳዩ እንደሚችሉ መገመት ያስፈልጋል፡፡

ማንኛዋም ሴት የወር አበባዋ በሚቀርበት ጊዜ ገና ከጅምሩ ወደሐኪም ዘንድ ቀርባ ምርመራዋን ብትጀምር ሁኔታው አደጋ ከማስከተሉ በፊት እርምጃ ለመውሰድ ያስችላል እንደ ዶ/ር መብራቱ ጀምበር የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት ማብራሪያ፡፡ ለእርጉዝ ሴቶች ሊነገሩ የማይገባቸው ነገሮች፡- እርግጠኛ ነሽ ...መንታ ላለማርገዝሽ? አንቺ ...ሆድሽ ሊፈነዳ ደርሶአል እኮ...ከዚህ በላይ መቆየት የምትችይ ይመስልሻል? የእኔ ሚስት አኮ አምስት ልጅ ወልዳለች፡፡ ግን እንዳንቺ ሰውነቷ አልተበላሸም፡፡ ለመሆኑ ሐኪምሽ ምን ይልሻል? በእርግጥ ሙሉ በሙሉ ጤነኛ ነሽ? አትናደጂ፡፡ ግን እርግዝና ነው ወይንስ ሌላ ነገር? መልክሽ እንዲህ የጠቆረው በጤና ነው? መልክሽ እንዲህ እስኪጠፋ ድረስ ያሳበጠሽ በእርግጥ እርግዝናው ብቻ ነው? አንቺ...ምን መሰልሽ? ምነው እርግዝናው ቢቀርስ? ...ወዘተ ከላይ የተጠቀሱትንና መሰል ነገሮችን ለእርጉዝ ሴቶች ማቅረብ ተገቢ አይደለም፡፡ በተለይም አርግዞ በመውለድ ዙሪያ ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን ከመንገር ይልቅ ሴትየዋ በትክክል ወደሐኪም ሄዳ እርዳታ ማግኘት የምትችልበትን መንገድ መምከር ይገባል፡፡

Read 19253 times
Administrator

Latest from Administrator