Saturday, 15 June 2013 11:38

ዘ ሮክ የአመቱ ትርፋማ ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዘ ሮክ ዘንድሮ በተወነባቸው ፊልሞች ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማስገኘት የሚስተካከለው አለመገኘቱን ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘገበ፡፡ ፕሮፌሽናል የነፃ ትግል ስፖርተኛ የሆነውና በሙሉ ስሙ ድዋይን ጆንሰን ተብሎ የሚታወቀው ዘ ሮክ፣ ላለፉት 16 ሳምንታት በቦክስ ኦፊስ የገቢ ደረጃ ከአንድ እስከ 10 ባለው ቦታ ባለመጥፋት ስኬታማነቱን አረጋግጧል፡፡ በ2013 ለእይታ የበቁት ዘ ሮክ የተወነባቸው ፊልሞች ‹ስኒች›፤ ‹ጂ.አይ. ጆ ሪታልዬሽን›፤ ‹ፔይን ኤንድ ጌይን› እና ሰሞኑን መታየት የጀመረው ‹ፋስት ኤንድ ፊርዬስ 6› ናቸው፡፡ በገቢ በጣም ስኬታማ የሆነባቸው ሁለቱ ፊልሞች በመላው ዓለም 365.53 ሚሊዮን ዶላር ያስገባው ‹ጂ.አይ. ጆ ሪታልዬሽን› እና 586.66 ሚሊዮን ዶላር ያስገኘው ‹ፋስት ኤንድ ፊርዬስ 6› ይጠቀሳሉ፡፡ በተወነባቸው ፊልሞች ገበያው ለምን እንደተሟሟቀለት የተጠየቀው ተዋናዩ በሰጠው ምላሽ ባለፉት 13 ዓመታት በትዋናው በመስራት ከፍተኛ ጥረት እና ትጋት እንደነበረው ገልፆ “ከፍተኛ ስኬት የማስመዝገብ ግብ ነበረኝ” ሲል ተናግሯል፡፡

Read 1887 times