Saturday, 15 June 2013 11:29

የ“ሉሲ” አካዳሚ ተማሪዎች በየክፍላቸው ቤተመፃሕፍት አቋቋሙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የሉሲ አካዳሚ ተማሪዎች በየክፍላቸው ንዑስ ቤተመፃሕፍት አቋቋሙ። የሕፃናትንና ታዳጊ ወጣቶችን የንባብ ባህል ለማዳበር የተቋቋሙትና ትላንት የተመረቁት የየክፍሉ አብያተ መጻሕፍት በዝነኛ ሰዎች ስም ተሰይመዋል። ከ1ኛ-5ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ያቋቋሙት ቤተመጻሕፍት በደራሲ ሜሪ ጃፋር ስም የተሰየመ ሲሆን ቤተመጻሕፍቱን ደራሲ ሜሪ ጃፋር መርቀውታል፡፡ በክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል የተሰየመውን የ7ኛ ክፍል ቤተመፃህፍት ደግሞ ኢንጂነር ታደለ ብጡል ሲመርቁት በደራሲና ጋዜጠኛ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር የተሰየመውን የ11ኛ ክፍል ቤተመፃህፍት ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ መርቀውታል። ለ12ኛ ክፍል የሚያገለግሉት ሁለት አብያተ መጻሕፍት በክብርት ዶ/ር ስንዱ ገብሩ እና በደራሲ ፀሐይ መላኩ፣ የተሰየሙ ሲሆን አምባሳደር ዶ/ር ሳሙኤል አሰፋና ደራሲ ፀሐይ መላኩ መርቀውታል፡፡ ትምሕርት ቤቱ ካሉት 18 መማርያ ክፍሎች ስድስቱ በዚህ መልኩ ቤተመጻሕፍት ያገኙ ሲሆን የሌሎችም እንደሚቀጥል ማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1542 times