Saturday, 15 June 2013 11:27

“ፍልስምና ፫” እና “ኢትዮጵያ…” ለንባብ በቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በጋዜጠኛ፣ ደራሲና ጸሐፌ ተውኔት ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ የተዘጋጀው “ፍልስምና ፫” የተሰኘው መፅሃፍ ለንባብ በቃ፡፡ በቃለ ምልልስ መልክ በተዘጋጀው መጽሐፍ ውስጥ ስምንት ባለሙያዎች የተካተቱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ኬሚካል ኢንጂነር ጌታሁን ሄራሞ፣ በቀለማት ፍልስፍናና ሥነ ልቦናዊ ማንነታቸው፣ ተፊሪ ንጉሤ በገዳ ሥርአት፣ በዋቂፈናና ኢሬቻ፣ ዶ/ር መስፍን አርአያ በማንነታችን ላይ የተናገሩት ይገኝበታል፡፡ 144 ገፆች ያሉት መጽሐፍ በ32 ብር እየተሸጠ ነው፡፡

በሌላ በኩል በግዛው ዘውዱ የተዘጋጀው “ኢትዮጵያ፣ ታሪክ፣ ትርክትና ታሪካችን” መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በ285 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፍ በፋርኢስት ትሬዲንግ የታተመ ሲሆን በ60.70 ብር እየተሸጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ መጽሐፉ በማጣቀሻነት ከተጠቀማቸው በርካታ ዋቢዎች መካከል የአለቃ ደስታ ተክለወልድ፣ የፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ የነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ፣ የአሌክሳንደር ቡላቶቪችና የዶናልድ ሌቪን መጻሕፍትና ሌሎች ጽሑፎች ይገኙበታል፡፡

Read 1659 times