Saturday, 15 June 2013 11:23

ኤፍኤም አዲስ ነገ የ13ኛ ዓመት በዓሉን ያከብራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮጵያ የመጀመርያው የኤፍኤም ሬዲዮ ጣቢያ ኤፍኤም አዲስ 97.1 የተመሰረተበትን 13ኛ ዓመት በዓል ነገ ከጧቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በሐራምቤ ሆቴል እንደሚያከብር አስታውቋል፡፡ የ24 ሰዓት ስርጭት ያለው ብቸኛው የኢትዮጵያ ሬዲዮ ጣቢያ፣ ነገ በሚያከብረው በዓል ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ታደሰ ዝናዬ “የኤፍ ኤም ጣቢያዎቻችን ለሕብረተሰብ ሁለንተናዊ እድገትና ለሀገር ልማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እና ጉድለቶቻቸው” በሚል ርእስ እንዲሁም የጣቢያው ጋዜጠኛ አቶ ዮናስ ወልደየስ “ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ከየት ወደየት?” በሚሉ ርእሶች ጥናታዊ የውይይት ፅሁፍ ያቀርባሉ፡፡ በውይይት ላይ ከ100 በላይ ተጋባዥ እንግዶች እንደሚገኙ የታወቀ ሲሆን ጣቢያው ከበዓሉ በኋላ የአንድ ዓመት ተኩል ጥናት ያደረገበትን የዝግጅቶች ለውጥ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 2889 times