Wednesday, 12 June 2013 14:56

“... ከማህጸን ውጪ እርግዝና... ”

Written by 
Rate this item
(4 votes)

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ 1% የሚሆኑት እርግዝናዎች ከማህጸን ውጭ ሊፈጠሩ የሚችሉ እርግዝናዎች ናቸው፡፡ እርግዝናው ከዘር ማስተላለፊያ ቱቦ በተጨማሪ የሆድ እቃ ውስጥ ጭምር ሊፈጠር ይችላል፡፡ ቢሆንም ግን 1% ከሚሆኑት ከማህጸን ውጭ እርግዝናዎች 98% ያህሉ የሚቆዩት እዚያው የዘር ማስተላለፊያ ቱቦ ውስጥ ነው፡፡ ከማህጸን ውጭ የሚከሰት እርግዝና የሚያጋጥማቸው ሴቶች በእድሜ ከ35 -49 አመት“” ድረስ ያሉ ናቸው፡፡ ከማህጸን ውጭ እርግዝናን አመላካች የሚሆኑ የህመም አይነቶች ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌም ... የታችኛው የሆድ ክፍል ላይ ከበድ ያለ ህመም መሰማት፣ ሽንትን በመሽናት ጊዜ የህመም ስሜት፣ የማህጸን በር መድማትና ...ሌሎችም ናቸው፡፡ ከላይ የተጠቀሰውን ርእሰ ጉዳይ በሚመለከት አንዲት ጉዳት የገጠማት ሴት እንዲህ ትላለች፡፡ “”...እኔ በእድሜዬ ወደ ሰላሳ ስድስት አመት እጠጋለሁ፡፡ እኔ በልጅነ ወለድ ወለድ አድርጌ የሶስት ልጆች እናት ነኝ፡፡

ከዚህም በሁዋላ ልጅ መውለድ አልችልም ...አልፈልግም ብዬ ባለቤንም አሳምኜ በመኖር ላይ ነበርኩ፡፡ ታድያ አንድ ቀን አመሻሹ ላይ እንዲያው ድካም ድካም ይሰማኝ ጀመር፡፡ ወደ ሶስት ሰአት ከምሽቱ ሲሆን ዝም ብዬ ወደ አልጋዬ ሄድኩኝ፡፡ ከተወሰነ መኝታ በሁዋላ ...የሆነ... ስሜት ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ፡፡ ወዲያው ቀና ስል ሰውነ በደም ተጨ ማልቆአል፡፡ በድንጋጤ ስጮህ ባለቤ ተነስቶ እፍስፍስ አድርጎ ወደሆስፒታል ወሰደኝ፡፡ እኔ ለጊዜው እራሴን አላውቅም ነበር፡፡ ድንጋጤውና የህመሙ ስሜት ተደማምሮ እራሴን እንደመሳት ብዬ ነበር፡፡ በሁዋላም አስፈላጊው ሕክምና ተደ ርጎልኝ ሲሻለኝ የሆንኩትን ነገር ጠየቅሁ፡፡ ለካንስ ከማህጸን ውጪ እርግዝና የሚባል ነገር ነው፡፡ በጣም ነው ያዘንኩት፡፡ ሐኪሞቹም ከዚህ በላይም ለጉዳት ትጋለጪ ነበር የሚል ነበር መልሳቸው...” ስሜን አትግለጹ ከማህጸን ውጭ እርግዝና በሚለው ጉዳይ መልስ እንዲሰጡ ለዚህ እትም የተጋበዙት ዶ/ር መብራቱ ጀምበር የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት እና በብራስ የእናቶችና የህጻናት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ናቸው፡፡

እንደ ዶ/ር መብራቱ ማብራሪያ ይህ የጤና እክል በተለምዶ ከማህጸን በላይ እርግዝና ቢባልም ትክክለኛ ስያሜው ግን ከማህጸን ውጭ እርግዝና በእንግሊዝኛው (Ectopic pregnancy) ይባላል፡፡ ከማህጸን ውጭ እርግዝና ቃሉም እንደሚያስረዳው እርግዝናው በትክክለኛው ተፈጥሮ አዊ ቦታው ማለትም በማህጸን ውስጥ ሳይሆን ከማህጸኑ ውጭ ባሉ አካላት ላይ እንዲሁም በሆድ እቃ ላይ የሚፈጠርበት አጋጣሚ ይከሰታል፡፡ ይህ እርግዝና ብዙ ጊዜ ዘለቄታ የለውም፡፡ እንደሚታወቀው እርግዝና የሚፈጠረው በወንዱ ዘርና በሴቷ ዘር ግንኙነት መንስኤነት ነው፡፡ ይህ በጤናማ መልኩ የተፈጠረ ከሆነ የሚገኘው በዘር ማስተላለፊያ ቱቦው ላይ ነው፡፡ በዚያም የተወሰነ ቀን ካሳለፈ በሁዋላ የተወሰነ የሰውነት ገንቢ ሕዋሳቶች ደረጃ ላይ ሲደርስ ወደ ዋናው የማህጸን ክፍል ውስጥ ይገባል፡፡ በማህጸን ውስጥም እርግዝናው እስኪጨርስ እና አድ ጎም ለመወለድ እስኪደርስ ድረስ ይቆያል፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ይህ ሂደት ሊዛባ ይችላል፡፡

በዚህም ሳቢያ ጽንሱ ወደ ማህጸን ከመሄዱ ይልቅ የተለያየ ቦታ በመቅረት ባለበት ቦታ እድገቱን ይጀምራል፡፡ በተለይም በዘር ማስተላለፊያ ቱቦው ጫፍ ወይንም መሃል አለበለዚያም ወደ ማህጸን ተጠግቶ ሊያድግ ይችላል፡፡ ከዚህም ውጭ ጽንሱ እንደተፈጠረ ዝም ብሎ ሆድ እቃ ውስጥ በመውደቅ ሞራ ላይ ወይንም አንጀት ላይ እና በመሳሰሉት አካላት በመጠጋት በዚያው እድገቱን ሊጀምርም ይችላል፡፡ ዶ/ር መብራቱ በተጨማሪም እንዳብራሩት የወንድ እና የሴት የዘር ፍሬ ከተገናኙ በሁዋላ ወደትክክለኛው ማህጸን ከመግባት ይልቅ ወደተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ለማምራቱ በምክንያትነት የሚጠቀሱ ሁኔታዎች አሉ፡፡ ከዚህም ዋነኛው የዘር ማስተላለፊያው ቱቦ ክፍት መሆኑ ነው፡፡ የዘር ማስተላለፊያ ቱቦው ከእንቁላሉ ተጠግቶ ያለ ሲሆን ወደ እንቁላሉ በመሄድ እንቁላሉን ይቀልባል፡፡ በመሀከላቸው ባለው ክፍተት አማካኝነትም እንቁላሉ ከቦታው በሚወጣ በት ጊዜ ተቀብሎም ወደ ዋናው ማህጸን ያመጣዋል፡፡ ይህንን በምሳሌ ለመረዳትም አሉ ዶ/ር መብራቱ ...የዘር ማሰተላለፊያው ቱቦ የሚሰራውን ስራ ከጉሮሮ ጋር ማነጻጸር ይቻላል፡፡

ጉሮሮ ምግብን ተቀብሎ ወደ ሆድ እቃ እንደሚያስተላልፈው ሁሉ የዘር ማስተላለፊያው ቱቦም ወደ ማህጸን በማምጣት ላይ ባለበት ጊዜ የወንድ የዘር ፈሳሽ ደግሞ ከብልት ወደ ውስጥ ሲፈስ መስመር ላይ የወንዱና የሴት የዘር ፍሬዎች እንዲገናኙ ምክንያት ይሆናል፡፡ ከተወሰነ ደረጃ በሁዋላም ወደዋናው ማህጸን በመግባት ፋንታ እዚያው ዘር ማስተላለፊያ ቱቦው ላይ ተጣብቆ የመቅረት ወይንም ወደ ሆድ እቃ የመግባት የመሳሰሉት ችግሮች ሲደርሱ ይስተዋላሉ፡፡ ይህንን ችግር ከሚያስከትሉት መካከል ፡- የማህጸን ቁስለት ኢንፌክሽን፣ የዘር ማስተላለፊያ ቱቦ ተፈጥሮአዊ እውክታ ..ወዘተ ይገኙበታል፡፡ ከላይ እንደተጠቀሱት ያሉ አጋጣሚዎች ዘር ከተፈጠረ በሁዋላ ወደትክክለኛው ቦታ ለመም ጣት በሚያደርገው እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታን አያገኝም፡፡ በተለይም እያደገ በመጣ ቁጥር መጠ ኑም እየጨመረ ስለሚመጣ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ስለሚቸገር እዚያው እነበረበት ቦታ ይቀጥ ላል፡፡ ጽንስ ሲፈጠር አብረው የሚፈጠሩ ነገሮች አሉ፡፡ ለምሳሌም እንግዴ ልጅ ፣የሽርት ውሀ እና የመሳሰሉት ነገሮች በማህጸን ውስጥ የጽንሱ አካል በመሆን ጊዜው እስኪያበቃ ድረስ እድ ገቱን እየተቆጣጠሩ ምግብ እየመገቡ አየር እንዲኖረው አስችለው በስተመጨረሻው ልጁ ይወለ ዳል፡፡

ከማህጸን ውጪ እርግዝና በሚሆንበትም ጊዜ ጊዜው ወይንም እድገቱ እስከፈቀደ ድረስ ምንም ባልተጉዋደለ መልኩ ሁሉም ነገሮች በየደረጃቸው አብረው ይፈጠራሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ግን እንዳለበት ቦታ ይወሰናል፡፡ ዘር ከተፈጠረ በሁዋላ በዘር ቱቦው ውስጥ በመጀመሪያው በመሀ ሉና በስተመጨረሻው ባለው ቦታ እንደየጥበት እና ስፋታቸው የመለጠጥ አቅማቸው እንደፈቀደ እድገቱን ይዘው ሊቀጥሉ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ጥበቱ እየተባባሰ በሚሄድበት ጊዜ ቱቦው ስለሚፈነዳ ደም በሴትየዋ ሆድእቃ ውስጥ ይፈሳል፡፡ ያን ጊዜ ሴትየዋ ችግር ላይ ትወድቃለች፡፡ በኢትዮጵያ በህብረተሰቡ ዘንድ አንድ ጥሩ ያልሆነ ልምድ አለ፡፡ አንዲት ሴት እርጉዝ ነኝ ብላ ቤተሰብዋን ወይንም ጉዋደኞቿን ስታማክር ሶስት ወር ሳይሞላት ወደሐኪም ቤት ሄዳ ምርመራ እንዳትጀምር የሚያደርጉ ምክሮች ይሰጡዋታል፡፡ ነገር ግን ይህ በፍጹም ትክክል እንዳልሆነ ሁሉም ሰው ሊገነዘበው ይገባል፡፡

አንዲት ሴት እንዲያውም ወደሐኪም ቤት ሄዳ ምክር መጠየቅ እና ምርመራ ማድረግ ያለባት ከእርግዝና አስቀድሞ ሲሆን የወር አበባ ከቀረበት ጊዜ ጀምሮ ግን ወደሀኪም መቅረብ ግዴታ መሆን አለበት፡፡ አስቀድሞ ምርመራ ከተጀመረ እርግዝናው በትክክለ ኛው ሁኔታ ይሁን አይሁን በአልትራሳውንድ ጭምር በማየት ማወቅ የሚቻልበት የህክምና ዘዴ አለ፡፡ ስለዚህ ማንኛዋም ሴት ችግር ላይ ከመውደቅዋ አስቀድሞ እርምጃ ለመውሰድ ቀላል ይሆናል፡፡ ከማህጸን ውጪ እርግዝና ከሁለት እስከሶስት ወር ድረስ አደጋው ይከሰታል፡፡ አልፎ አልፎ ግን በሆድ እቃ ውስጥ የተረገዘው ጽንስ በተለይም ቀደም ባለው ጊዜ እስኪወለድ ድረስ ማደግ መቻሉን መረጃዎች ይጠቁማሉ ብለዋል ዶ/ር መብራቱ ጀምበር ፡፡ ይቀጥላል

Read 12644 times