ለሩሲያዊው ባለቅኔ አሌክሳንደር ፔትሮቪች ፑሽኪን፣ ሦስት ቶን ክብደት ያለው ግዙፍ የነሐስ ሐውልት በአዲስ አበባ ሣር ቤት አካባቢ በሚገኘው “ፑሽኪን አደባባይ” ሊቆምለት እንደሆነ የሩሲያ የሳይንስ እና ባህል ማእከል አስታወቀ፡፡ ማእከሉ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፣ የነሐስ ሐውልቱ በአፍሪካ አህጉር በግዙፍነቱ ተወዳዳሪ የሌለው ሲሆን በታዋቂው ሩስያዊ ቀራፂ ዲሚትሪ ኩኮለስ ተቀርፆ በሞስኮ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈላጊውን ትብብር እያደረጉልን ነው ያሉት የማዕከሉ ዳይሬክተር፣ የፑሽኪንን ኢትዮጵያዊ ቅድመ አያት አብርሃም ጋኒባልን ያካተተው ሃውልት፣ በጣም ያጌጠና የውጭ ጐብኝዎችን ጭምር የሚስብ እንደሆነ ገልፀውልናል፡፡ የፑሽኪን ልደት በዚህ ሳምንት በሩስያ፣ በኢትዮጵያ እና በተቀረውም ዓለም እየተከበረ ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል