በወጣት ገጣሚያን እየተሰናዳ የሚቀርበው “ግጥም በጃዝ” 23ኛ ወርሃዊ ዝግጅቱን እንደሚያቀርብ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ በመጪው ረቡዕ ማምሻውን 11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል በሚቀርበው ዝግጅት ላይ ግሩም ዘነበ፣ በረከት በላይነህ፣ ሜሮን ጌትነት፣ መንግስቱ ዘገየ፣ ዮሐንስ ሐብተማርያም በግጥም፤ የቀድሞው የአዲስ አበባ ከንቲባ አቶ ብርሃነ ደሬሳ “የአፍሪካ የነፃነትና አንድነት ትግል” በሚል ርእስ ዲስኩር እንዲሁም ሀብታሙ ስዩም ወግ ያቀርባሉ፡፡