ፒያሳ አካባቢ የሚገኘው “ኤልቤት ሆቴል” ወርሃዊ የኪነጥበብ ዝግጅት ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡ የዛሬ ሳምንት በሆቴሉ የሚጀመረው ዝግጅት ግጥም ላይ የሚያተኩር ነው ብሏል - ሆቴሉ፡፡ መድረክ ያላገኙ እና የራሳቸውን ግጥም የሚያቀርቡ ከሕፃናት እስከ አረጋውያን ሥራዎች ላይ እናተኩራለን ያሉት የሆቴሉ ሥራ አስኪያጅ፣ አንጋፋ ገጣሚያንም ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በሀዲስ አለማየሁ “ፍቅር እስከ መቃብር” መጽሐፍ ውስጥ ያሉ ግጥሞች በመክፈቻው እለት እንደሚቀርቡ ጠቁመዋል፡፡