Print this page
Wednesday, 12 June 2013 14:06

ተዋናዩ በግብር እዳ ፈረንሳዊ ዜግነቱን ሊፍቅ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ጄራርድ ዴፓርዲዮ በፈረንሳይ መንግስት በተጠየቀው የግብር እዳ በመማረር ፓስፖርቱን በመመለስ ዜግነቱን ለመፋቅ እንዳሰበ “ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር” አስታወቀ፡፡ ‹ለስ ሚዝረብልስ› በተባለው ፊልም ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፈው ተዋናዩ፤ 1.3 ሚሊዮን ዶላር የግብር እዳ አለበት በሚል የፈረንሳይ መንግስት ክስ መስርቶበታል፡፡ ክሱ በአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፍራንስዋ ሆላንዴ ድጋፍ ማግኘቱ ተዋናዩን እንዳበሳጨው ታውቋል፡፡ ከትወና ሙያው ባሻገር በፊልም ሰሪነት፤ በነጋዴነት እና በወይን እርሻ ባለቤትነት የሚታወቀው የ64 ዓመቱ ዴፓርዲዮ በሙያ ዘመኑ 17 ፊልሞች ላይ ሰርቷል፡፡

ከፈረንሳይ መንግስት ጋር የገባው እሰጥ አገባ ያማረረው ተዋናዩ፤ ኑሮውን በቤልጂዬም ለማድረግ ወስኗል ተብሏል፡፡ ከተመሰረተበት ክስ ጋር በተያያዘ በፓሪስ ከተማ ያለው 85 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ግዙፍ ቤቱ ሐራጅ ሊወጣበት እንደሚችል ተዘግቧል፡፡ ጄራርድ ጄፓርዲዬ ከሁለት ሳምንት በፊት የሩሲያ መንግስት በፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አማካኝነት የራሽያ ዜግነት እንደሰጠው የገለፀው “ዘ ሆሊውድ”፤ በቺቺኒያ ታሪክ ዙርያ በሚሰሩ ሁለት የራሽያ ፊልሞች ላይ እየተወነ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ተዋናዩ የራሽያ ዜግነቱን ካገኘ በኋላ ከሚያስገባው ገቢ እጅግ ያነሰ ግብር የሚከፍልበት እድል ማግኘቱን እንደገለፀ የዘገበው መፅሄቱ፤ በሞስኮ ከተማ ሬስቶራንት ለመክፈት ማቀዱን ይፋ እንዳደረገም አውስቷል፡፡

Read 1840 times
Administrator

Latest from Administrator