Print this page
Saturday, 01 June 2013 14:03

“የመንፈስ ከፍታ” ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በገጣሚና ጋዜጠኛ በረከት በላይነህ የተፃፈው “የመንፈስ ከፍታ” የተሰኘ የግጥም መድበል ሰኞ በ11፡30 በዋቢሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡ በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፋፈለው “የመንፈስ ከፍታ”፡ የገጣሚው 48 ያህል ወጥ ግጥሞችና፣ ጃላላዲን ሩሚን ጨምሮ ሌሎች የታወቁ የፋርስ ገጣሚያን የፃፏቸው 31 ትርጉም ግጥሞች ተካተውበታል፡፡ በምረቃ ስነስርአቱ ላይ ታዋቂ ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የመጽሐፉ ዋጋ 30 ብር ነው፡፡ ገጣሚው በቅርቡም “ንፋስ አፍቃሪዎች” የተሰኘ የግጥም ሲዲ አሳትሞ ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡

Read 1943 times
Administrator

Latest from Administrator