Saturday, 01 June 2013 13:57

የዓለም ሃብታሙ የኤሌክትሮኒክስ ሙዚቃ ዲጄ ታወቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከኤሌክትሮኒክስ ሙዚቃ ዲጄዎች፣ ሆላንዳዊ ዲጄ ቲዬስቶ 75 ሚሊዮን ዶላር መሪነቱን እንደያዘ ሴለብሪቲ ኔትዎርዝ ገለፀ። ለግሉ በገዛው ጄት አውሮፕላን በመላው ዓለም በመዘዋወር የሚሰራው የ44 ዓመቱ ዲጄ ቲዬስቶ፣ በአማካይ ለአንድ ምሽት ስራ እስከ 250ሺ ዶላር እየተከፈለው ባለፈው ዓመት ብቻ ሃያ ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። ቲዮስቶ፣ በሙዚቃ መሸጫ ሱቅ እየሰራና ፒዛ እየተላላከ ይኖር እንደነበር አስታውሶ፣ ዲጄነትን የጀመረ ጊዜ ባንድ ምሽት ሃምሳ ዶላር ብቻ ይከፈለው እንደነበር ገልጿል።

ከዲጄነት ጎን ለጎን፣ እንደ ሌሎቹ ዲጄዎች በሙዚቃ ፕሮዲውሰርነትና በአቀናባሪነት እየሰራ አምስት ሙሉ አልበሞችን እና ሶስት የሪሚክስ አልበሞችን ለገበያ አብቅቷል፡፡ ባንድ ምሽት በአማካይ ከ100ሺ እስከ 500ሺ ዶላር ከሚከፈላቸው ታዋቂ የኤሌክትሮኒክስ ሙዚቃ ዲጄዎች መካከል አንዳንዶቹ፣ የግል ጄት አውሮፕላንና ውድ ቪላ እየገዙ ለቅንጦት ኑሮ ገንዘባቸውን ሲያፈሱ ይታያሉ። ሴሌብሪቲ ኔትዎርዝ ባወጣው የዲጄዎች ደረጃ፣ ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ የወጡት ከሃምሳ እስከ ስድሳ ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ሃብት ያላቸው ዲጄዎች ናቸው።

Read 2505 times