Saturday, 01 June 2013 12:38

የሞባይል ደንበኞች ከውጪ ሀገር በሚደወሉ ቁጥሮች እየተጭበረበሩ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች በውጪ ሃገር የስልክ ቁጥሮች በሚደወሉ ጥሪዎች እየተጭበረበሩ ናቸው ያለው ኢትዮቴሌኮም፣ ደንበኞቹ ጥሪውን አንስተው እንዳይመልሱ አሳሰበ፡፡ መስሪያ ቤቱ ከደንበኞች የደረሰውን ጥቆማ በማጣራት ለማጭበርበር የሚደውልባቸው የውጪ ሃገር ስልክ ቁጥሮች መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ያላቸው የሚከተሉት ናቸው -+35418441045፣ +4238773310፣ +34518441045፣ +4238773952፣ +004238773395፣ 004238773740፣ 004238773050 እንዲሁም 0025270300504፡፡

እነዚህ ቁጥሮች የተደወለለት ደንበኛ ጥሪዎቹን ካነሳና ካነጋገረ የአገልግሎቱ ሂሳብ በእሱ እንደሚታሰብ አረጋግጫለሁ ብሏል ኢትዮ ቴሌኮም፡፡ በተጨማሪም በአጭር የጽሑፍ መልዕክት “እጣ ደርሶዎታል” በማለት ነው በ0037178912368 ቁጥር የሚላክ መልእክት የተጭበረበረና ሃሰተኛ መሆኑን ደንበኞቼ ይወቅልኝ” ብሏል፡፡ ደንበኞች በ0042፣ 0025፣ 0022፣ 0023፣ 0037 እና 0043 በሚጀምሩ የውጪ ሃገር የስልክ ቁጥሮች ለሚደወሉላቸው ጥሪዎች ማንኛውም አይነት ምላሽ እንዳይሰጡ ኢትዮ ቴሌኮም አሳስቧል፡፡

Read 2437 times