Print this page
Monday, 27 May 2013 15:15

ቦሊውድ 100ኛ ዓመቱን እያከበረ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በዓመት ከ1500 በላይ ፊልሞች ሰርቶ ለዕይታ በማቅረብ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የሚያገኘው የህንዱ የፊልም ማዕከል ቦሊውድ፤ ሰሞኑን 100ኛ ዓመቱን እያከበረ ነው፡፡ የማዕከሉ ፊልሞች ዓለም አቀፍ ገበያ በየዓመቱ 10 በመቶ በማደግ ላይ እንደሚገኝ ያመለከተው “ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንድያ” የተባለ ጋዜጣ፤ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የፊልሞቹ አመታዊ ገቢ 3.85 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ ይችላል ብሏል፡፡ የቦሊውድ 100ኛ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ የወጡ ዘገባዎች እንደሚሉት፤ ፊልሞቹ ገቢያቸው እንዲጨምር የመላውን ዓለም ፍላጎት ባማከለ መልኩ መሰራት ያለባቸው ሲሆን የህንድ መንግስት በአክሽን እና በወሲባዊ ፊልሞች ላይ የሚያደርገውን የበዛ ሴንሰርሺፕ መቀነስ ይኖርበታል፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፤ አብዛኞቹ የቦሊውድ ፊልሞች አማካይ በጀት 1.5 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን በከፍተኛ የጥራት ደረጃ ለዓለም አቀፍ ገበያ የሚሰሩት ደግሞ በአማካይ እስከ 20 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይመደብላቸዋል፡፡

በህንድ ፊልሞች ላይ የሚሳተፉት ህንዶች ብቻ ሲሆኑ ለወንድ ተዋናዮች ትልቁ ክፍያ በአንድ ፊልም እስከ 16 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን ለሴቶች ደግሞ 1.5 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ ለፊልሞች ስራ የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ረገድ የህንድ ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት እንዲሁም በማከፋፈል ስራ ላይ የተሰማሩ የግል ኩባንያዎች ትልቅ ሚና አላቸው፡፡ የመጀመርያው የቦሊውድ ፊልም እ.ኤ.አ በ1913 ዓም ለእይታ የበቃው “ዳዳሼብ ፓላኬ” የተሰኘ ባለጥቁር እና ነጭ ቀለም ድምፅ አልባ ምስል ነው፡፡

Read 3603 times
Administrator

Latest from Administrator