Monday, 27 May 2013 15:12

የመላ አፍሪካ “ቪዥዋል አርት” ጉባዔ እየተካሄደ ነው

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(0 votes)

የአፍሪካ ሕብረት በቀድሞ ስም የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የተመሠረተበትን ሃምሳኛ ዓመት በማስመልከት የተዘጋጀ የመላ አፍሪካ ቪዥዋል አርት ጉባኤ እየተካሄደ ነው፡፡ ትናንት ጧት ተከፍቶ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ በሚጠበቀው ጉባዔ ላይ ርእሰ ጉዳዩን የተመለከቱ 17 ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚቀርቡ አዘጋጁ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሥነጥበባት ኮሌጅ አስታውቋል፡፡ የኮሌጁ ዲን መምህር አርቲስት ነብዩ ባዬ ለአዲስ አድማስ ጉዳዩን አስመልክቶ ሲናገሩ፣ የአፍሪካ አንድነት ከቅኝ አገዛዝ ለመላቀቅ በተደረገ ፖለቲካዊ ትግል ብቻ የመጣ ሳይሆን የኪነጥበባትም ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን አስታውሰው “Pan African Performing and visual Art” በሚል ጭብጥ የሚካሄደው ጉባዔ በሥእል፣ በትያትር፣ በሙዚቃ፣ በሥነጽሑፍና በሌሎች ኪነጥበባዊ ዘርፎች የነበሩ አበርክቶዎች በጥናቶቹ እንደሚዳሰሱ ጠቅሰዋል፡፡ አቶ ነብዩ በተያያዘም በአፍሪካ ሥነጽሑፍ ከፍተኛ ድርሻ የነበረውና ከትናንት ወዲያ የቀብር ሥነሥርአቱ የተከናወነው ናይጄሪያዊ የአፍሪካ እንግሊዝኛ ሥነጽሑፍ አባት ቺንዋ አቼቤን ለመዘከር ከአንጋፋው ደራሲ ስራዎች የተወሰዱ ታሪኮች በትወና እንደሚቀርቡ ተናግረዋል፡፡

Read 1895 times