Saturday, 11 May 2013 13:55

“የፊልም ድርሰት አፃፃፍ ብልሃት” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(42 votes)

በአዲስ ተስፋ የተዘጋጀ “የፊልም ድርሰት አፃፃፍ ብልሃት” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሰሞን ለንባብ በቅቷል፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጀዋሬ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ “የአገራችን የፊልም ኢንዱስትሪ በእውቀት የሚጽፉ ሙያተኞች እጅጉን ያስፈልጉታል፡፡

አሁን አሁን በፊልም ጥበብ ላይ የተዘጋጁ መፃሕፍት ታትመው ለንባብ እየበቁ ነው… የፈጠራ ጽሑፍ ተሰጥኦ እያላቸው አቅጣጫው (ቴክኒኩ) ለጠፋቸው ሁሉ እነሆ አቅጣጫው እላለሁ” ብለዋል፡፡ መጽሐፉ ከያዛቸው አብይ ርዕሰ ጉዳዮች መካከል “የድራማ ምንነትና ታሪክ”፣ “ፊልም ምንድነው?” “ፊልም እንዴት ይፃፋል” እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ በ171 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ በ55 ብር እየተሸጠ ነው፡፡

Read 15536 times Last modified on Monday, 13 May 2013 09:25