Saturday, 11 May 2013 11:08

ካፒታል ሆቴልና ስፓ ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ባለ 5 ኮከቡ ካፒታል ሆቴልና ስፓ ትናንት ተመርቆ አገልግሎት ጀመረ፡፡ በ172 ሚሊየን ብር የተሠራው ሆቴሉ 114 የመኝታ ክፍሎች አሉት፡፡ በአቶ የማነ ገ/ሥላሴ ባለቤትነት የተገነባው ይኼ የግል ሆቴል መዋኛ፣ የሴቶችና የወንዶች መታሻ ክፍሎችና መዋቢያ፣ አንድ ፎቅ ጂምናዚየም፣ ባር፣ ላውንጅ፣ የስብሰባ አዳራሾች አሉት፡፡ ግንባታው አምስት ዓመት የፈጀው ሆቴል፤ በማስፋፊያው ባለ 11 ፎቅ ሕንፃ እያስገነባ ሲሆን ከምድር በታች ሁለት ፎቅ የመኪና ማቆሚያ አለው፡፡

ሆቴሉ በአሁኑ ወቅት ለ225 ዜጐች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን የሠራተኞቹን ቁጥር 270 የማድረስ ዕቅድ አለው፡፡ አቶ የማነ ገ/ሥላሴ የሆሲ ትሬዲንግ ሃውስ ባለቤት ሲሆኑ ድርጅታቸው አሉ ከሚባሉት የገቢና ወጪ ንግድ ድርጅቶች አንዱ ነው፡፡ ሆሲ በብረታ ብረት ማሽኖች፣ መሳሪያዎችና ሌሎች ተዛማጅ ንግዶች ላይ የተሰማራ ሲሆን፤ የእርሻ ምርት ውጤቶችንም ለውጭ ገበያዎች በማቅረብ ይታወቃል፡፡

Read 5643 times Last modified on Monday, 13 May 2013 09:23