የበይነ መረብ (internet) አጠቃቀምን አስመልክቶ የተዘጋጀው መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በዓለም ደገፋ እና ወንድወሰን አሰፋ የተዘጋጀው “በይነመረብ” የተሰኘ መጽሐፍ በዘርፉ ያሉትን የእንግሊዝኛ ቃላትና ሐረጐች በአማርኛ ቃላት ለመተካት የተሞከረበት ነው፡፡ አስራሰባት ምእራፎች ያሉት መጽሐፍ በበይነመረባዊ የቃላት መፍቻ የታገዘ ነው፡፡ ከ185 ገፆች በላይ ያሉት መጽሐፍ በ50 ብር እየተሸጠ ነው፡፡