Saturday, 27 April 2013 12:02

“የራስ አሽከር” ፊልም ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሀዋስ ፋሚሊ ፊልም፤ “የራስ አሽከር” የተሰኘ አዲስ የቤተሰብ ልብ ሰቃይ ፊልም በነገው እለት በ8,፣10 እና 12 እንደሚያስመርቅ አስታወቀ፡፡ በአዲስ አበባና በግል ሲኒማ ቤቶች የሚመረቀውን የ100 ደቂቃ ፊልም የፃፈው ዘካርያስ ካሳ ነው፡፡ ሰርቶ ለማጠናቀቅ ሃያ ዘጠኝ ወራት የፈጀው ፊልም፤ ቀረፃ የተከናወነው በአዲስ አበባ፣ በደብረዘይትና በደቡብ ክልል እንደሆነ ታውቋል፡፡ በፊልሙ ላይ ሽመልስ አበራ (ጆሮ)፣ ዝናህብዙ ፀጋዬ፣ ቶማስ ቶራ፣ ዳንኤል ሙሉነህ፣ እሱባለው ተስፋዬ፣ ትዕግስት ዋሲሁን፣ ወንድወሰን ብርሃኑ (ዶክሌ)፣ አንዱአለም ሽፈራው እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡

Read 3108 times