Print this page
Saturday, 20 April 2013 12:36

የኃይለመለኮት መዋዕል “እንካስላንቲያ” ለንባብ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአንጋፋው ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል የተዘጋጀ “እንካስላንቲያ” የተሰኘ መፅሃፍ ሰሞኑን ለንባብ ቀረበ፡፡ ደራሲው ስለ መፅሃፉ ፋይዳ በገለፀበት መግቢያ፤ “የእንካስላንቲያ ሥነ-ቃል የግጥማዊ ዜማነት ባህሪይ ስላለው ወጣቶች እየተፈራረቁና እየተፎካከሩ በመሳተፍ አያሌ ቁምነገሮችን … ይማሩበታል” ብሏል፡፡

በ107 ገፆች የተቀነበበው መፅሃፉ፤ ዕውቀት፣ ዲሞክራሲ፣ ሙስና፣ ፍትህ ወዘተ በሚሉ ርዕሶች ስር የተዘጋጁ እንካስላንቲያዎችን የያዘ ሲሆን በ20 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ኃይለመለኮት መዋዕል “ጉንጉን” እና “የወዲያነሸ” በተባሉት ተወዳጅ የረዥም ልብወለድ ሥራዎቹ ይታወቃል፡፡

Read 2648 times
Administrator

Latest from Administrator