Monday, 15 April 2013 09:19

አርቲስቱ በታይላንድ እንዲታከም ተወሠነ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አርቲስት ፍቃዱ አያሌው ባጋጠመው የነርቭ ህመም ወደ ታይላንድ ባንኮክ ሄዶ ህይወቱን የሚታደግ ህክምና እንዲያገኝ በህክምና ባለሙያዎች ተወሰነ፡፡ የሰዓሊው ጓደኖችና ወዳጅ ዘመዶች በውጭ አገር በሚያደርገው ህክምና ጥሪ ለማሰባሰብ እያስተባበሩ ናቸው፡፡ ሰዓሊ ፍቃዱ የነርቭ ህመሙ ለመታከም አዲስ አበባ ለሚገኘው የሚዮንግ ሰንግ ሆስፒታል ቆይታ ቢኖረውም ሙሉ ለሙሉ ሊፈወስ አልቻለም፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የስነጥበብ ትምህርት ቤት በማዕረግ የተመረቀው አርቲስት ፍቃዱ አያሌው በዳንዲቦሩ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመምህርነት አገልግሏል፡፡ለሰዓሊው የውጭ ሀገር ህክምና ድጋፍ ለሚያደርጉ ሁለት የሞባይል ስልክ ቁጥሮች 0911742168 እና 0919193132 መጠቀም የሚቻል ሲሆን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአካውንት ቁጥር 1000031068 437 መላክ እንደሚቻል አስተባባሪዎቹ ገልፀዋል፡፡

Read 2856 times Last modified on Thursday, 18 April 2013 06:21