Monday, 15 April 2013 09:18

ቅዱስ ያሬድ በተለያዩ ዝግጅቶች ይዘከራል

Written by 
Rate this item
(9 votes)

የኢትዮጵያ የዜማ አባት የሚባለው ቅዱስ ያሬድ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተዘከረ ሲሆን አዲስ አበባ የሚገኘው የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስትያን፤ የዜማ አባቱ የተወለደበትን 1500ኛ የልደት በዓል ነገ ከረፋዱ አራት ሰዓት እንደሚያከብር አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አዲሱ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንደሚገኙ በሚጠበቅበት በዓል፤ “በቅዱስ ያሬድ ታሪክ እና ሥራዎች” ላይ ውይይት ይካሄዳል ተብሏል፡፡

ፒያሳ አካባቢ የሚገኘው ኤልቤት ሆቴል ከዚሁ ልደት ጋር በተያያዘ የቅዱስ ያሬድ ዜማዎች በተባበሩት መንግስታት የባሕል ቅርስ ሆነው መመዝገባቸውን አስመልክቶ ዝግጅት እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት በሚቀርበው ዝግጅት፤የቅዱስ ያሬድ ቤተክርስትያን ዘማሪዎች ያሬዳዊ ዜማ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡

Read 5158 times