Print this page
Monday, 15 April 2013 07:46

የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ተነሱ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት በመሆን ለረጅም ጊዜ ያገለገሉት አቶ ኡሞድ ኡቦንግ ከክልል ፕሬዚዳንትነታቸው ተነስተው በፌደራል መንግስት መመደባቸው ታወቀ፡፡ ሰሞኑን በክልሉ በተካሄዱ ተከታታይ የስራ አስፈፃሚ፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ እና የተለያዩ የስራ ሃላፊዎች ስብሰባ ላይ አቶ ኡሞድ ከክልል ፕሬዚዳንትነታቸው በመነሳት በፌደራል መንግስት በስራ ሃላፊነት መዛወራቸውን መግለፃቸውን ምንጮቻችን አመልክተዋል፡፡ ቀጣዩ የክልሉ ፕሬዚዳንት በሚቀጥለው ሳምንት በሚካሄድ ጉባኤ እንደሚመረጥ እና የአቶ ኡሞድ ኦቦንግ ከክልሉ ፕሬዚዳንትነት መነሳት በይፋ እንደሚነገር ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የክልሉ የስራ ሃላፊ ተናግረዋል፡፡

አቶ ኡሞድ በየትኛው የፌዴራል መንግስት መስሪያ ቤት እንደተመደቡ አለመታወቁንና የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንትና የድርጅቱ ሊቀመንበር በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ጋት ሉዋክ፤ ቀጣዩ የክልሉ ፕሬዚዳንት እንደማይሆኑ በስፋት እየተነገረ መሆኑን ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ አቶ ኡሞድ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከመሆናቸው በፊት የክልሉ የፀጥታ ሃላፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡

Read 3628 times
Administrator

Latest from Administrator