Print this page
Monday, 08 April 2013 11:45

“የዳንኤል ክብረት ዕይታዎች” 3ኛ አመቱን ያከብራል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተለያዩ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ዙርያ መጣጥፎች የሚያቀርብበት “የዳንኤል ዕይታዎች” የጡመራ መድረክ (Blog) የተመሠረተበት ሶስተኛ አመት ሚያዚያ 5 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ አክሱም ሆቴል አዳራሽ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄድ ፕሮግራም እንደሚከበር ተገለፀ፡፡ በዕለቱ በሚካሄደው ፕሮግራም ላይ “የዳንኤል እይታዎች” ጡመራ ላይ የቀረቡ ጽሑፎች ቅኝት፣ የኢትዮጵያውያን ማህበራዊ ድረ ገፆች ዳሰሳ፣ የማህበራዊ ሚዲያ ህጋዊና ሥነ ምግባራዊ ሃላፊነት በሚሉና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ዙርያ ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚቀርቡና ሰፊ ውይይት እንደሚካሄድም የፕሮግራሙ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ትውልድን በመቅረጽ ለሀገርና ለህዝብ የሚበጁ በጐ ሥራዎች የሚያከናውኑና ሃሳብ የሚያመነጩ ግለሰቦችና ተቋማት እውቅናና ሽልማት እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፤ ደራሲና የቤተክርስቲያን ተመራማሪ ሲሆን፤ 16 መፃሕፍትን በግሉ፣ ሶስት መፃሕፍትን ከሌሎች ጋር ለህትመት አብቅቷል፡፡ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ መጣጥፎችንም በጋዜጦችና መፅሄቶች ላይ አስነብቧል፡፡

Read 6134 times
Administrator

Latest from Administrator