Monday, 08 April 2013 11:40

ራፕሮች ወደ ንግዱ እያዘነበሉ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታዋቂ ራፕሮች ከተለያዩ ኩባንያዎች ጋር በሚሰሯቸው የስፖንሰርሺፕ ውሎች እና ማስታወቂያዎች ሃብታቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን ሴለብሪቴኔትዎርዝ አስታወቀ፡፡ የራፕ ሙዚቃን መጫወት፤ ማሳተም እና የተለያዩ የሙዚቃ ዝግጅቶችን በማቅረብ የሚገኘው ገቢ እጅግ እያነሰ መምጣቱን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ሴሌብሪቲ ኔትዎርዝ ከሙዚቃ ውጭ የእውቅ ራፕሮች ገቢ በጣም እያደገ መምጣቱን ያመለከተው የ2013 የዓለም ራፕሮች የሃብት ደረጃን ሰሞኑን ይፋ ሲያደርግ ነው፡፡ ሲን ኮምበስ ወይም ፒዲዲ ባለፈው አንድ አመት በሃብቱ ላይ ተጨማሪ 80 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል ያለው ሴሌብሪቲ ኔትዎርዝ 580 ሚሊዮን ዶላር አስመዝግቦ በአንደኝነት እንደሚመራ ገልጿል፡፡

ለፒዲዲ ሃብት ማደግ ከአልኮል መጠጦች አንዱ ከሆነው የቮድካ አልኮል ብራንድ ሲሮክ የተባለ ምርት ላይ በሚሰራው ንግድ ሽያጭ በመድራቱ ነው ያለው ሴሌብሪቲ ኔትዎርዝ ራፕሩ ይህን ኩባንያ ቢሸጥ እስከ 150 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ገቢ ሊያገኝ እንደሚችል ጠቁማል፡፡ ባለፈው አንድ ዓመት በሃብቱ ላይ ተጨማሪ 25 ሚሊዮን ዶላር የጨመረው ጄይዚ በ500 ሚሊዮን ዶላር የሃብት ግምቱ ሁለተኛ ደረጃ ሲይዝ፤ ቢትስ ባይ ድሬ በተባለ የጆሮ ማዳመጫ ምርቱ ያለፈውን አንድ አመት 100 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሰብስቦ የሃብት መጠኑን 360 ሚሊዮን ዶላር ያደረሰው ዶር ድሬ ሶስተኛ ሆኗል፡፡ ሌሎች ራፕሮች ማስተር ፒ በ350 ሚሊዮን ዶላር፤ ሴንት በ260 ሚሊዮን ዶላር፤ በርድ ማን በ150 ሚሊዮን ዶላር፤ ኤሚነም በ140 ሚሊዮን ዶላር፤ ስኑፕ ዶግ በ130 ሚሊዮን ዶላር፤ አይስ ኪውብ በ120 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ሊል ዋይኔ በ110 ሚሊዮን ዶላር የሃብት መጠን እስከ 10 ያለውን ደረጃ አግኝተዋል፡፡

Read 2321 times