Saturday, 30 March 2013 16:02

የብራዚል ባህል ፌስቲቫል ነገ ይጠናቀቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አዲስ አበባ የሚገኘው የብራዚል ኤምባሲ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀውና ከየካቲት 22 ጀምሮ ሲካሄድ የሰነበተው የብራዚል የባህል ፌስቲቫል ነገ በኤምባሲው በሚቀርብ የሙዚቃ ዝግጅት ይጠናቀቃል፡፡ የካቲት 22 ቀን 2005 ዓ.ም ሸራተን አዲስ በሼፍ ክርስቲያኖ ላና፤ በሸራተን አዲስ በቀረበና ለስምንት ቀናት በዘለቀ የምግብ ፌስቲቫል የተጀመረው ዝግጅት፤ ከመጋቢት 2 እስከ መጋቢት 7 በቆየ የፊልም ፌስቲቫለ የቀጠለ ሲሆን “The Passion of Brazilian Football” በሚል ርእስ መጋቢት 11 የጀመረው የፎቶግራፍ አውደርእይም ዛሬ ይዘጋል፡፡ የኤምባሲው አንደኛ ፀሐፊ እና የባህል አታሼ ሚስተር ማርሴሎ ቦርሄስ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ዛሬ ማታ በኤምባሲው የሚደረገውን መዝጊያ ፊደል የሙዚቃ ባንድ ያቀርባል፡፡

Read 3072 times