Print this page
Monday, 25 March 2013 11:13

አርቲስቶችን እናክብራቸው፤ ቤተሰብ አላቸው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ሳምንት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ እትም ላይ በአርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ ዙሪያ የቀረበውን አጭር ዜና ስመለከት ብዙ ሃሳቦች መጡብኝ፡፡ በእርግጥ ሠራዊት ፍቅሬ የተወራበት ነገር አሉባልታ እንደሆነ መግለፁ በዜናው ተዘግቧል፡፡ ነገር ግን ሁለት ቅሬታዎች አሉኝ፡፡ አንደኛው ቅሬታዬ በዜና አዘጋገቡ ላይ ነው፡፡ ሁለተኛው ቅሬታዬ ግን በዜና ዘገባው ላይ ሳይሆን፣ በጊዜው በአርቲስቶች ላይ በሚናፈሱ ወሬዎች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያ ቅሬታዬን ላስቀድም፡፡ በአዲስ አድማስ የቀረበውን አጭር ዜና፣ በሙያ መመዘኛ እንየው ከተባለ ተቃራኒ ገፅታዎች ይስተዋሉበታል፡፡ ብልሃትና ጥንቃቄ የተሞላበት ዘገባ ነው፡፡

“ብልጠትም ያለበት ይመስላል” ብዬ ስሜታዊ ድምዳሜ ላይ መድረስ አልፈልግም፡፡ ጠንቃቃ ዜና መሆኑን ግን ያለ ጥርጥር መናገር ይቻላል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በዜናው አንዳንድ ገፅታዎች ላይ ግልፅ ጉድለቶች አሉበት፡፡ ለምሳሌ ዜናው ብዙ መረጃዎችን የሚሰጥ ይመስላል፡፡ ይህም የጥንቃቄ ውጤት ሳይሆን አይቀርም፡፡ ነገር ግን ዜናው ከሚሰጠን መረጃ ይልቅ በርካታ መልስ የሌላቸው ጥያቄዎችን የሚፈጥርብን መሆኑ ትልቅ ጉድለት ነው፡፡ ሌላኛው ጉድለት፣ በዜናው ርእስ ላይ ጭምር የሚታይ ነው፡፡

ለዜናው መነሻ የሆነው ወሬ በዜናው ውስጥ ተጠቅሷል፡፡ አንዲት ሴት፣ አርቲስቱ ሊስመኝና ሊደባብሰኝ ሞክሯል ብላለች የሚል ወሬ ነው መነሻው፡፡ እንግዲህ ከዚህ ልንገነዘብ የምንችለው ወሬው ስለ ወሲብ ትንኮሳ እንጂ ስለ መድፈር ሙከራ አለመሆኑን ነው፡፡ ደግሞም ወሬው አሉባልታ መሆኑንም አርቲስቱ ገልጿል፡፡ በሌላ አነጋገር፤ ወሲባዊ ትንኮሳ እንደፈፀመ ተደርጐ ሲናፈስ የቆው ወሬ አሉባልታ እንደሆነ አርቲስቱ ተናግሯል፡፡ የዜናው ርእስ ግን “የወሲብ ትንኮሳ” የሚል አገላለፅን ሳይሆን፣ “የመድፈር ሙከራ” የሚል ሀረግ ተጠቅሟል፡፡ ይሄ ጉድለት ነው፡፡

Read 4547 times
Administrator

Latest from Administrator