Monday, 25 March 2013 11:11

‹‹አርሾ›› የሕክምና ላብራቶሪ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ተሰጠው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

‹‹አርሾ›› የተሰኘው የግል የሕክምና ላቦራቶሪ አገልግሎት ሰጪ ድርጅት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ ድርጅቶችንና አገልግሎቶችን ጥራትን ማዕከል በማድረግ እያወዳደረ ዕውቅና በመስጠት ከሚታወቀው “Business Initiative Directives” ከሚባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት “Century International Quality ERA Award in Gold Category” በሚለው የሽልማት ዘርፍ እ.ኤ.አ. በመጋቢት 10 ቀን 2013 ዓ.ም በአዉሮፓ የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ማዕከል በኾነው በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በተካሄደው ሥነ-ሥርዓት የወርቅ ዋንጫና የዕውቅና ሰርቲፍኬት ተሰጠው፡፡

የላብራቶሪው ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ቀዲዳ ለአዲስ አድማስ እንደገለጹት፤ከ173 አገራት በተለያየ የግል የሥራ ዘርፍ ጥራትና ብቃት ያለው አገልግሎት በመስጠት በአየር መንገድ፣ በኢንጂነሪንግ፣ በሕትመት ሥራ፣ በፖሊስ አገልግሎት፣ በሕክምና እና በተለያዩ ሥራዎች ዘርፍ ተሰማርተው ሲሠሩ የነበሩ የተመረጡ ድርጅቶች በፕላቲኒየም፣ በወቅርና በብር ምድብ የተለያየ ሽልማት በተቀበሉበት መድረክ ላይ ‹‹አርሾ›› ተካፋይ ሆኖ በመሸለሙ እጅግ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

አክለውም “ሽልማቱ አሁን ከምንሰጠው ብቃት ያለው ሥራ የበለጠ እንድንተጋ ያደርገናል” ብለዋል፡፡ ኤርቫቢር ቲርዚያ በተባሉ አርመናዊ ፋርማሲስት በአነስተኛ ደረጃ ተመስርቶ ሥራ ከጀመረበት ከ1963 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይ ቀደም ሲል ምንም የግል የሕክምና አገልግሎት ባልተስፋፋበትና አንድም የግል ላቦራቶሪ አገልግሎት ባልነበረበት ጊዜያት ከኢትዮጵያ ጤናና ስነምግብ ኢንስቲትዩት ቀጥሎ ለሁሉም የመንግሥት፤ የድርጅቶችና የግል የጤና ተቋሞች አስተማማኝ የላቦራቶሪ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶአል፡፡ራሱን በማሳደርግም የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመከተል እየሰጠ ባለው አገልግሎት ለዚህ ሽልማት የበቃው ‹‹አርሾ የሕክምና ላቦራቶሪ በአሁኑ ሰአት በአዲስ አበባ ስድስት ቅርንጫፎችን በመክፈት አየሠራ ይገኛል፡፡

Read 3251 times