በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን የሕዳሴ ግድብ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ረቡዕ በ11 ሰዓት በብሄራዊ ትያትር የሥነፅሁፍ ምሽት ሊያቀርብ ነው፡፡ የማህበሩ ፕሬዚደንት ደራሲና ሃያሲ ጌታቸው በለጠ እንደገለፁት፤ አንጋፋ ደራስያን በአባይ ዙሪያ የገጠሟቸው ግጥሞች በምሽቱ ይዳሰሳሉ፡፡ ከዚህም በተማሪ ጥንታዊ የቆሎ ተማሪዎችና አባይ ያላቸውን መስተጋብር የሚቃኝ ዝግጅትም ተካትቷል፡፡ በተመሳሳይ ዜና የኢትዮጵያ ሰዓሊያን ማህበር በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ የሥዕል አውደርእይ በቅርቡ ያዘጋጃል ተብሏል፡፡