Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Monday, 07 November 2011 13:16

ጀስቲን ቢበር በገቢም በተወዳጅነትም እየመራ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በዩቲውብ 2 ቢሊዮን ተመልካች በማግኘት አዲስ ሪከርድ ያስመዘገበው ዝነኛው ዘፋኝ ጀስቲን ቢበር፤ ‹ቤቢ› በተሰኘ የሙዚቃ ቪድዮው ከፍተኛ ተመልካች እንዳገኘ ተገለፀ፡፡ “ማይ ዋርልድ 2.0” የተባለ አልበሙን የለቀቀው የ17 ዓመቱ ካናዳዊ አርቲስት፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በመላው አለም 12 ሚሊዮን የአልበሞቹን ቅጂ ሸጧል፡፡ በሳምንቱ አጋማሽ “አንደር ሚስሌትዎ” የተሰኘ አዲስ አልበሙን የለቀቀው ቢበር፤ በፈረንጆች አዲስ ዓመት (2012) ‹ቢሊቭ› በሚል ስያሜ ሌላ አዲስ አልበም ለመልቀቅ በዝግጅት ላይ መሆኑንም አስታውቋል፡፡

በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ጀስቲን ቢበር ባለው እውቅና ከኦባማና ከዳይላማ መብለጡን ያመለከተው ዘ ኦብዘርቨር ጋዜጣ፤ በፌስቡክ 36 ሚሊዮን አድናቂዎች፤ በትዊተር ደግሞ 13 ሚሊዮን ተከታዮችን እንዳፈራ ጠቅሷል፡ በዩቲውብ ከሚታዩ የቪድዮ ምስሎች የዘመኑ ምርጥ ድምፃውያን 86 በመቶ ድርሻ እንደያዙ የጠቆመው ጋዜጣው፤ በየሁለት ቀኑ የ48 ሰዓታት የቪድዮ ምስሎች የሚጫንበት የአርቲስቱ ድረገፅ በየቀኑ 3 ቢሊዮን ተመልካች ይጎበኘዋል፡፡ ጀስቲን ቢበር እድሜያቸው ከ30 በታች ከሆኑ ዝነኞች በሚያገኘው የክፍያ መጠን ሁለተኛ ደረጃ መያዙን ያመለከተው ፎርብስ መፅሄት በበኩሉ ባለፉት 12 ወራት 53 ሚሊዮን ዶላር መስራቱን አስታውቋል፡፡ በ3ዲ የተሰራው “ጀስቲን ቢበር፡ ኔቨር ሴይ ኔቨር” የተሰኘው ጥናታዊ ፊልሙ የ100 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ ማስገኘቱ ለገቢው ማደግ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳበረከተ ታውቋል፡፡

 

Read 3237 times Last modified on Monday, 07 November 2011 13:18

Latest from