Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Monday, 07 November 2011 13:11

ኤሚ ዋይን ሃውስ ከሞተች በኋላ 3ኛ አልበሟ ሊወጣ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሟቿ ኤሚ ዋይን ሃውስ 3ኛ አልበም ‹ላዮነስ፡ ሂድን ትሬዠርስ› በሚል ስያሜ ከወር በኋላ ለገበያ ሊበቃ ነው፡፡ በአይስላንድ ሪከርድስ የተዘጋጀው አልበሙ 12 የኤሚ አዳዲስ ዘፈኖችን ያካትታል፡፡ ኤሚ ዋይን ሃውስ ከልክ ባለፈ አልኮል መጠጥ ተመርዛ በ27 ዓመቷ ድንገት ህይወቷ እንዳለፈ በምርመራ መረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ከሞተች ከ3 ወር በኋላ ለገበያ በሚበቃ ስራዋ ከሟች የዓለማችን ምርጥ ሙዚቀኞች ተርታ የሚያሰልፍ ገቢ እንደምታገኝ ተጠብቋል፡፡ ለገበያ ከቀረበ 2ኛ ዓመቱን የያዘው የኤሚ ዋይን ሃውስ “ባክ ቱ ብላክ” የተባለ አልበም ከሞተች በኋላ በወር ውስጥ 175ሺ ቅጂ ተሸጧል፡፡ ከሞታቸው በኋላ ከፍተኛ ገቢ ያገኙ ሙዚቀኞችን ዓመታዊ የገቢ ደረጃ ከሳምንት በፊት ያወጣው ፎርብስ መፅሄት፤ አንደኛው 170 ሚሊዮን ዶላር ያገኘው ማይክል ጃክሰን መሆኑን ሲያመለክት ኤልቪስ ፕሪስሊ በ55 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ፤ የቢትልሱ ጆን ሌነን በ12 ሚሊዮን ዶላር ሶስተኛ እንዲሁም ጂም ሄንድሪክስ በ7 ሚሊዮን ዶላር ገቢ 5ኛ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

Read 2842 times