Monday, 04 March 2013 00:00

እናት ባንክ ሥራ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ሁለንተናዊ አቅም የሚያሻሽሉና ከዚህ ቀደም በኢንዱስትሪው ትኩረት ያልተሰጣቸውን አገልግሎቶች ይዞ ሥራ መጀመሩን እናት ባንክ አስታወቀ፡፡ 

ባንኩ አገልግሎት የሚጀምርባቸው የመጀመሪያዎቹ ቅርንጫፎች ባንቢስ አካባቢ ከዮርዳኖስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው ዋና መ/ቤቱና ቦሌ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አካባቢ መሆኑ ታውቋል፡፡ የባንቢስ አካባቢው ዓቢይ ቅርንጫፍ በእቴጌ ጣይቱ ስም የተሰየመ ሲሆን የቦሌ መድኃኒዓለሙ በንግሥተ ሳባ እንዲሁም የሰንጋ ተራው በወ/ሮ አበበች ጎበና ስም መሰየማቸውን ገልጸዋል፡፡ 

እናት ባንክ የሴቶችን አቅም በማጐልበትና በመጠቀም በኢንዱስትሪው ፈጣን ዕድገት ለማምጣትና የአገሪቱን ዕድገት ቀጣይ ለማድረግ የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ አስታውቋል፡፡

Read 3697 times