Saturday, 23 February 2013 11:48

“ከመጠን በላይ” ፊልም ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ቴዲ ሊ ጽፎ ያዘጋጀውና ሊ ፔፕ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበው “ከመጠን በላይ” የፍቅር ፊልም ነገ ከሰዓት በኋላ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች ይመረቃል፡፡ የ102 ደቂቃ ያለውን ይሄን ፊልም ለመሥራት ዘጠኝ (?) መፍጀቱን ያመለከተው ሊፔፕ ፊልም ፕሮዳክሽን፣ ፊልሙ በስድስት ዓለምአቀፍ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ለመታየት መዘጋጀቱንና የተቀረፀበት ካሜራም SD Mark II canon መሆኑን ገልጿል፡፡ አጽመ ታሪኩን ባልተለመደ ውሳኔ ላይ ባደረገው የፍቅር ፊልም ላይ አማኑዔል ይልማ፣ ሄለን በድሉ፣ ሸዊት ከበደ፣ ኤልያስ ወሰንየለህ፣ ጋዜጠኛ መሳይ ወንድሜነህ፣ ቴዎድሮስ ጋሻው በዛና ሌሎችም በትወና፣ አማኑኤል ይልማና ሃይሉ አመርጋ (ጃኖ ባንድ) የማጀቢያ ሙዚቃ በመስራት፣ ቴዎድሮስ ወርቁ ፊልሙን ኤዲት በማድረግ ተሳትፈዋል፡፡

Read 3949 times