Print this page
Saturday, 16 February 2013 13:28

የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ መጽሐፍ ረቡዕ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አሁን በህይወት በሌሉት ታዋቂው ገጣሚ ዮሐንስ አድማሱ የተዘጋጀው “የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ አጭር የሕይወቱና የጽሑፉ ታሪክ” የተሰኘ መጽሐፍ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት ዝግጅት ተቋም የፊታችን ረቡዕ በ10፡30 በብሔራዊ ቴአትር እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ መጽሐፉን የገጣሚ ዮሐንስ አድማሱ ወንድም የሆኑትና ባለፈው ሳምንት ሕይወታቸው ያለፈው ዶ/ር ዮናስ አድማሱ ኤዲት እንዳደረጉት ታውቋል፡፡ በመጽሐፉ ምረቃ ዕለት ከዮፍታሔ ንጉሤ ሥራዎች ተቀንጭበው የሚቀርቡ ሲሆን፤ ዮፍታሔ የደረሰውን “አፋጀሽኝ” ትያትርን ለመጀመሪያ ጊዜ የተወኑት አቶ በለጠ ገብሬ ይገኛሉ፡፡ ከአቶ በለጠ ሌላ አርቲስት ሃይማኖት አለሙ በመርሃ ግብር አስተዋዋቂነት፣ ደራሲና ሃያሲ አቶ አስፋው ዳምጤ እና ፕሮፌሰር ሺፈራው በቀለ ስለ መጽሐፉ አስተያየት፣ ፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ ስለ ሕትመቱ እንዲሁም ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 3754 times
Administrator

Latest from Administrator