Saturday, 09 February 2013 12:38

“ውቢት እንቅልፋሟ” የልጆች ትያትር ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“ውቢት እንቅልፋሟ” የሚል የልጆች ትያትር ዛሬ ከጧቱ 3 ሰዓት በኤድናሞል ሲኒማ እንደሚያስመርቅ ናታን መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን አስታወቀ፡፡ ትያትሩን ፅፎ ያዘጋጀው አብነት ጌታቸው ሲሆን በትያትሩ ምረቃ ላይ አዱኛ የዳንስ ቡድን ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡በየትምህርት ቤቱ በመዞር የሚታየው ይኼው ትያትር፣ ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል የሚማሩ ሕፃናትን በማለም የተሰራ ነው፡፡ ትያትሩ በናታን መልቲ ሚዲያ “የተራኪ ዳንሰኛና ድራማ ክለብ” መዘጋጀቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

Read 3578 times